Uncategorized

የሞሮኮ አየር መንገድ ለዛሬ ተይዘው የነበሩ በረራዎችን ለመሰረዝ ተገዷል

ምክንያቱ ደግሞ አብራሪዎቹ የስራ ማቆም አድማ በመምታታቸው ነው ብሏል የሞሮኮ ሮያል አየር መንገድ በድረ ገጹ ባሰራጨው ጽሁፍ፡፡
ሚድል ኢስት ሞኒተር እንደዘገበው አብራሪዎቹ ስራ ለማቆም ያስገደዳቸው ላቀረቡት የደሞዝና ሌሎች ጥቅማጥቅሞች ጥያቄ ከአሰሪ ድርጅታቸው አጥጋቢ መልስ አለማግኘታቸው ነው፡፡
በድርጅቱና በሰራተኞቹ መካከል ለወራት የዘለቀ ድርድር ቢደረግም መግባባት አልተቻለም ብለዋል የአብራሪዎች ማህበር አመራሮች፡፡
አየር መንገዱም ሰራተኞቹ ወደ ስራ ገበታቸው በፍጥነት እንዲመለሱና የተስተጓጎለው የበረራ አገልግሎት እንዲጀመር ለማህበሩ ጥሪ ከማቅረብ በዘለለ ስለጥያቄያቸው የሠጠው ማብራሪያ የለም፡

Related Articles

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Back to top button