EconomyEthiopiaPolitics

በኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ የተመራው የማክሮ ኢኮኖሚ ኮሚቴ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳለፈ፡፡

የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ፍፁም አረጋ እንደገለፁት ኮሚቴው በስብሰባው የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡ በዚህም መሠረት፦
1. የአገር ውስጥ የግል ባንኮች ከብሄራዊ ባንክ ለሚገዙት “27% ቦንድ” ብሄራዊ ባንክ የሚከፍላቸው ወለድ አሁን ካለው ከ3% ወደ 5% ከፍ እንዲል፣
2. የኢትዮጵያ ዳያስፖራ በአገር ውስጥ ባንኮች በውጭ ምንዛሪ የሚያስቀምጡት የ50,000 የአሜሪካን ዶላር ገደብ እንዲነሳ፣
3. የግል ባንኮች የውጭ ምንዛሪ ግኝታቸውን 30% ለብሄራዊ ባንክ የሚሸጡበት ተመን በመግዢያና በመሸጫ መካከል ባለ (አማካይ) ዋጋ እንዲሆን፣
4. በውጭ ምንዛሪ ክፍያ እንዲቀበሉ የተፈቀደላቸው የንግድ ድርጅቶች በስራ ላይ ካለው ዝርዝር በተጨማሪ:-
* በኤርፖርት ውስጥ የሚሰጥ የቴሌኮም አገልግሎት፣
* ለውጭ ቱሪስቶች የቻርተርድ አገልግሎት የሚሰጡ የግል አየር መንገዶች፣
* የውጭ ዜጎችን የሚያስተናግዱ የእንግዳ ማረፊያዎች፣
* የውጭ ዜጎችን የሚያስተናግዱ ልዩ ክሊኒኮች እና
* የውጭ ዜጎችን የሚያስተናግዱ ሆስፒታሎችን እንዲጨምር ኮሚቴው መወሰኑንም አቶ ፍፁም ተናግረዋል።
ኤፍ ቢ ሲ

አርትስ 24/12/2010

Related Articles

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Back to top button