EthiopiaSocial

ጠ/ሚኒስትር ዶ/ር አብይ ሽልማት ተበረከተላቸው

አርትስ 05/13/2010
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል ላመጡት ሰላምና እርቅ ልዩ ሽልማት አበረከተች።

ቤተ ክርስቲያኗ ልዩ ሽልማቱን ያበረከተችው ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መካከል ብሎም በምስራቅ አፍሪካ ቀጠና ሰላም እንዲመጣ አድርገዋል በሚል ነው።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ሽልማቱን በተረከቡበት ወቅትም ሽልማቱ ያለእረፍት ይህ ነገር እንዲመጣ ሲታገሉ ለነበሩ እና ይህ ለውጥ እንዲመጣ ሲፀልዩ ለነበሩትን በሙሉ የሚገባ ነው ማለታቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ልዩ ሀላፊ አቶ ፍፁም አረጋ በትዊተር ገጻቸው አስታውቀዋል።

Related Articles

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Back to top button