EconomyEthiopiaPoliticsRegionsSocial

በአዲስ አበባ 161 ሺ ወጣቶችን ወደ ስራ ለማስገባት የተያዘው ዕቅድ የሚበረታታ ነው አሉ የአሜሪካው አምባሳደር ማይክ ሬይነር

አርትስ 14/02/2011

ምክትል ከንቲባ ኢንጅነር ታከለ ኡማ የአሜሪካውን አምባሳደር ማይክ ሬይነርን በፅ/ቤታቸዉ ተቀብለው አነጋግረዋል።በውይይታቸውም በአካባቢ ጥበቃ እና በደረቅ ቆሻሻ አወጋገድ ዙሪያ አሜሪካ የቴክኒክ ድጋፍለማድረግ ፍላጎት እንዳላት አምባሳደሩ ተናግረዋል።በተመሳሳይ የከተማ አስተዳደሩ 161 ሺ ወጣቶች በዚህ አመት ወደ ስራ ለማስገባት የያዘው እቅድ የሚበረታታ መሆኑን የተናገሩት አምባሳደሩ ለወጣቶቹስልጠና መስጠትን ጨምሮ የተለያዩ ድጋፎችን ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል ሲል የከንቲባ ፅ/ቤት አስታውቋል።ምክትል ከንቲባ ኢንጅነር ታከለ በበኩላቸው አዲስ አበባን የቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግአስተዳደሩ የእንጦጦ ተራራን መነሻ በማድረግ የቱሪዝም ማዕከል ለመገንባት የያዘውን ዕቅድ ለአምባሳደሩ አብራርተዋል።  ለዚህ ፕሮጀክት ስኬታማነትም በትብብር ለመስራት ስምምነት ላይ ደርሰዋል።

 

Related Articles

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Back to top button