EthiopiaNewsSocial

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ባለቤታቸው የዘውዲቱ መሸሻ የህፃናትና ቤተሰብ የበጎ አድራጎት ልማት ማህበርን በገና በዓል ዋዜማ ጎበኙ::

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው የዘውዲቱ መሸሻ የህፃናትና ቤተሰብ የበጎ አድራጎት ልማት ማህበርን በገና በዓል ዋዜማ ጎበተኝተዋል ::

ለህፃናቱም የትምህርት መርጃ መሳሪያዎች: ብርድ ልብስና አንሶላ አበርክተዋል::

ዐቢይ አሕመድ የእማማ ዘውዲቱን ጥረት በማድነቅ በየቀን ተቀን እንቅስቃሴያችን የልግስናን ባህል እናዳብር ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል::

በተጨማሪም እማማ ዘውዲቱ የበለጠ ህፃናትን መርዳት እንዲችሉ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት እንዲረዷቸው አበረታትተዋል::

የዛሬ 27 አመት የተቋቋመው ማህበሩ ከሁለት መቶ በላይ ተንከባካቢ የሌላቸው ህፃናት መጠለያ ሲሰጥ ቆይቷል::

እማማ ዘውዲቱ በአሁኑ ወቅት 40 በማእከሉ ውስጥና 35 ከማእከሉ ውጭ ያሉ ህፃናት እርዳታ እየሰጡ ይገኛሉ::

በቅርቡ በግማሽ ክፍሉ ላይ የእሳት ቃጠሎ ቢደርስበትም ማእከሉ አገልግሎት መስጠቱን አላቆምም::

Related Articles

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Back to top button