SportSports

በጉጉት የተጠበቀውን የለንደን ደርቢ ጨዋታ አርሰናል ሲያሸንፍ፤ ሊቨርፑል መሪነቱን አስቀጥሏል


በጉጉት የተጠበቀውን የለንደን ደርቢ ጨዋታ አርሰናል ሲያሸንፍ፤ ሊቨርፑል መሪነቱን አስቀጥሏል

በእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ የ23ኛ ሳምንት መርሀግብር ጨዋታዎች በለንደን ደርቢ አርሰናል በኤምሬትስ ቼልሲን አስተናግዶ 2 ለ 0 ረትቷል::

አሌክሳንደር ላካዜት እና ሎረን ኮሽለኒ የድል ጎሎቹን አስቆጥረዋል ።

የጋለ ፉክክር በነበረው ጨዋታ ቀን ላይ ወልቭስ ሌስተርን 4 ለ 3 አሸንፏል ::

የሊጉ መሪ ሊቨርፑል አንፊልድ ላይ ክሪስታል ፖላስን ከመመራት ተነስቶ 4 ለ 3 አሸንፏል ። ለቀያዮቹ መሀመድ ሳላህ 2x፣ ሮቤርቶ ፊርሚኖ እና ሳዲዮ ማኔ ኳስን ከመረብ አገናኝተዋል::የኦሌ ጉናር ሶልሻዬር ማንችስተር ዩናይትድ በፖግባ እና ራሽፎርድ ጎሎች ብራይተነፈንን 2 ለ 1 አሸንፏል ።

በሌሎች ጨዋታዎች ኒውካስትል ካርዲፍን 3 ለ 0፤ በረንማውዝ 2 ለ 0 ዌስትሀም ፤ዋትፎርድ ከበርንሊ 0 ለ 0 ተለያይተዋል።

ዛሬ ቀን 10:30 ሀደርስፊልድ ታውን ከማንችስተር ሲቲ እንዲሁም ምሽት 1፡30 ፉልሀም ከቶተንሀም ይጫወታሉ  ።

ሊጉን ሊቨርፑልበ60 ነጥብ ይመራል ፤ ማ.ሲቲ በ53 ሁለተኛ፤ ቶተንሀም በ48 ሶስተኛ፤ ቼልሲ በ47 ነጥብ አራተኛ እንዲሁም አርሰናል እና ማ.ዩናይትድ በ44 ነጥብ አምስተኛና ስድስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል ።

 

 

Related Articles

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Back to top button