ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ በቫቲካን የሚገኘው የቅዱስ ስቴፋኖስ የአቢሲኒያ ቤተክርስቲያን ተገኝተዋል፡፡
ዶክተር አብይ በሮም ጉብኝታቸው ማጠናቀቂያ የሮማ ካቶሊክ ቤተክርስቲያንና የቫቲካን ራስ አገዝ ከተማ መሪ ቅዱስነታቸው አቡነ ፍራንሲስን አነጋግረዋል:: በተጨማሪም ከቅዱስ ከተማዋ ዋና አስተዳዳሪ ካርዲናል ፔትሮ ፓሮሊን ጋር በኢትዮጵያና በቫቲካን የጋራ ፍላጎቶች ላይ ተወያይተዋል::
ጠ/ሚር አብይ በቫቲካን የሚገኘውን የቅዱስ ስጢፋኖስ የአቢሲኒያ ቤተክርስቲያን ጎበኙ:: በጉብኝቱ ወቅትም በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል በጠ/ሚሩ አነሳሽነት የተገነባውን የሰላም ድልድይ ያስታወሱት ካርዲናል አባ ብርሃነ ኢየሱስ አቀባበል አድርገውላቸዋል::
ጠ/ሚር ዐቢይ አሕመድ በጣሊያኑ ጠ/ሚር ጁሴፔ ኮንቴ አቀባበል በፓላዞ ቺጊ/ብሄራዊ ቤተ መንግስት ተደረገላቸው:: ሁለቱ መሪዎች ባካሄዱት የሁለትዮሽ ውይይት ወቅትም ከአዲስ አበባ ምፅዋ በሚዘረጋው የባቡር ሃዲድ ዙሪያ ትብብራቸውን አንድ ደረጃ ከፍ ስለማድረግ ተወያይተዋል::
በጣሊያን የረጅም ጊዜ የልማት ትብብር መሰረትም ለትምህርት እድሜያቸው የደረሱ ህፃናትን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ፕሮግራሞች ላይ ለመስራት ተስማምተዋል::
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከዛሬ ጀምሮ በሚካሄደዉ የዳፎሱ የዓለም የኢኮኖሚ ፎረም ላይ እንደሚሳተፉ ታዉቋል፡፡