Politics

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የሚኒስትርና ተጠሪ መስሪያ ቤቶችን የ100 ቀናት እቅድ ግምገማ እየመሩ ነው

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በዛሬው እለት የቀጠለውን የሚኒስትርና ተጠሪ መስሪያ ቤቶችን የ100 ቀን እቅድ አፈፃፀም ግምገማ መርተዋል::

እንደዚህ ያሉ መድረኮች ለልምድ ልውውጥና መማማር ትልቅ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው አስምረውበታል ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ውይይትን በመሩበት ወቅት እንደተናገሩት የጋራ አገራዊ ራዕይን በተቀናጀ መልኩ ለማሳካት ግለሰቦችንና ተቋማትን ተጠያቂ ማድረግ ያስፈልጋል። ስለዚህም ተመሳሳይ ወቅታዊ የእቅድ አፈፃፀም ግምገማዎች ይካሄዳሉ::

ጠ/ሚር ዐቢይ አሕመድ ለውጥ ያሳዩ ሚኒስትርና ተጠሪ ተቋማትን በመጥቀስ ቅድሚያ የሚሰጣቸው ነጥቦች ላይ ቀጣይ አቅጣጫ ሰጥተዋል ብሏል የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት ።

Related Articles

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Back to top button