
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ለ6 ምሁራን የፕሮፌሰርነት ማዕረግ ሰጠ
ዩኒቨርሽቲዉ በትላንትናዉ ዕለት ለዶ/ር ሂሩት ወልደ ማርያምን፣ ለዶ/ር ተፈሪ ገድፍን ፣ ለዶ/ር ምሩፅ ግደይን ፣ ለዶ/ር ሃጎስ አሸናፊን፣ ለዶ/ር መረራ ጉዲናን እና ለዶ/ር ጌታቸው አሰፋን የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ሰጥቷል
የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ የተሰጣቸው 6 መምህራን እነማን ናቸዉ? በአጭሩ እነሆ፤-
- ፕሮፌሰር ሂሩት ወልደማርያም የመጀመርያ፣ ሁለተኛ እና የዶክትሬት ዲግሪያቸውን በቋንቋ ጥናት (Linguistics) ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ አግኝተዋል፡፡
ፕሮፌሰሯ በግላቸውና ከሙያ ጓደኞቻቸው ጋር በመሆን በጥናትና ምርምር የተሰሩ ከ6 በላይ ጥናታዊ ፅሁፎችን በታወቁ ሀገራዊና አለምዓቀፋዊ መፅሄቶች ላይ ለህትመት በማብቃት ከሚጠበቅባቸው 35 የህትመት ነጥብ 42 ነጥብ አስመዝገበዋል፡፡ በተጨማሪም በተለያዩ የዩኒቨርሲቲ ቦታዎች ላይ አገልግሎ የሰጡ ሲሆን ብዙ የማህበረሰብ አገልግሎቶችና የሙያ ነክ አስተዋጽኦ አድርገዋል:: ፕሮፌሰር ሂሩት ወልደማርያም በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በሂዩማኒቲስ፣ የቋንቋዎች ጥናት፣ የጆርናሊዝምና የኮሚዩኒኬሽን ኮሌጅ የቋንቋ ጥናት ትምህርት ክፍል ባልደረባ ሆነው በማገልገል ላይ ይገኛሉ።
- ፕሮፌሰር ተፈሪ ገድፍ የመጀመርያና ሁለተኛ ዲግሪያቸውን ዲግሪያቸውን በፋርማሲ (Pharmacy) ትምህርት ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ እንዲሁም የዶክትሬት ዲግሪያቸውን በፋርማሲ ትምህርት በጀርመን ከማርቲን ሉተር ዩኒቨርስቲ አግኝተዋል፡፡ ፕሮፌሰር ተፈሪ በግላቸውና ከሙያ ጓደኞቻቸው ጋር በመሆን በጥናትና ምርምር የተሰሩ ከ20 በላይ ጥናታዊ ፅሁፎችን በታወቁ ሀገራዊና አለምዓቀፋዊ መፅሄቶች ላይ ለህትመት በማብቃት ከሚጠበቅባቸው 35 የህትመት ነጥብ 104.56 ነጥብ አስመዝገበዋል፡፡ በተጨማሪም በተለያዩ የዩኒቨርሲቲ ቦታዎች ላይ አገልግሎ የሰጡ ሲሆን ብዙ የማህበረሰብ አገልግሎቶችና የሙያ ነክ አስተዋጽኦ አድርገዋል:: ፕሮፌሰር ተፈሪ ገድፍ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በጤና ሳይንስ ኮሌጅ የፋርማሲ ትምህርት ክፍል መምህር ሆነው በማገልገል ላይ ይገኛሉ።
- ፕሮፌሰር ምሩፅ ግደይ የመጀመርያ ዲግሪያቸውን በባዮሎጂ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ፣ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን በባዮዳይቨርሲቲ (Biodiversity) ከSwedish University of Agricultural Sciences፣ እንዲሁም የዶክትሬት ዲግሪያቸውን ቦታኒካል ሳይንስ (Botanical Science) ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ አግኝተዋል፡፡ ፕሮፌሰር ምሩፅ በግላቸውና ከሙያ ጓደኞቻቸው ጋር በመሆን በጥናትና ምርምር የተሰሩ ከ18 በላይ ጥናታዊ ፅሁፎችን በታወቁ ሀገራዊና አለምዓቀፋዊ መፅሄቶች ላይ ለህትመት በማብቃት ከሚጠበቅባቸው 35 የህትመት ነጥብ 56 ነጥብ አስመዝገበዋል፡፡ በተጨማሪም በተለያዩ የዩኒቨርሲቲ ቦታዎች ላይ አገልግሎ የሰጡ ሲሆን ብዙ የማህበረሰብ አገልግሎቶችና የሙያ ነክ አስተዋጽኦ አድርገዋል:: ፕሮፌሰር ምሩፅ ግደይ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በአክሊሉ ለማ የፓቶባዮሎጂ ኢንስቲትዩት (Aklilu Lemma Institute of Pathobiology) በእንዶድና ሌሎች የመድሃኒት ዕጽዋት የምርምር ማዕከል (Endod and Other Medicinal Plants Research Unit)ባልደረባ ሆነው በማገልገል ላይ ይገኛሉ።
- ፕሮፌሰር ሃጎስ አሸናፊ የእንስሳት ህክምና ዲግሪያቸውንና የሁለተኛ ዲግሪያቸውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ እንዲሁም የዶክትሬት ዲግሪያቸውን በቤልጄም ከሉቨን የካቶሊክ ዩኒቨርስቲ(Katholic University of Leuven)አግኝተዋል፡፡ ፕሮፌሰር ሃጎስ በግላቸውና ከሙያ ጓደኞቻቸው ጋር በመሆን በጥናትና ምርምር የተሰሩ ከ24 በላይ ጥናታዊ ፅሁፎችን በታወቁ ሀገራዊና አለምዓቀፋዊ መፅሄቶች ላይ ለህትመት በማብቃት ከሚጠበቅባቸው 35 የህትመት ነጥብ 94.06 ነጥብ አስመዝገበዋል፡፡ በተጨማሪም በተለያዩ የዩኒቨርሲቲ ቦታዎች ላይ አገልግሎ የሰጡ ሲሆን ብዙ የማህበረሰብ አገልግሎቶችና የሙያ ነክ አስተዋጽኦ አድርገዋል:: ፕሮፌሰር ሃጎስ አሸናፊ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በእንስሳት ህክምና እና ግብርና ኮሌጅ የፓቶሎጂና ፓራሲቶሎጂ (Pathology and Parasitology) ትምህርት ክፍል መምህር ሆነው በማገልገል ላይ ይገኛሉ።
- ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና የመጀመርያ ዲግሪያቸውን በፖለቲካ ሳይንስ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ፣ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን ከአሜሪካን ዩኒቨርስቲ ኢን ካይሮ (American University in Cairo)፣ እንዲሁም የዶክትሬት ዲግሪያቸውን በፖለቲካ ሳይንስ ከኢንስቲትዩት ኦፍ ሶሻል ስተዲስ (Institute of Social Studies) አግኝተዋል፡፡ ፕሮፌሰር መረራ በግላቸውና ከሙያ ጓደኞቻቸው ጋር በመሆን በጥናትና ምርምር የተሰሩ ከ12 በላይ ጥናታዊ ፅሁፎችን በታወቁ ሀገራዊና አለምዓቀፋዊ መፅሄቶች ላይ ለህትመት በማብቃት ከሚጠበቅባቸው 35 የህትመት ነጥብ 37.25 ነጥብ አስመዝገበዋል፡፡ በተጨማሪም በተለያዩ የዩኒቨርሲቲ ቦታዎች ላይ አገልግሎ የሰጡ ሲሆን ብዙ የማህበረሰብ አገልግሎቶችና የሙያ ነክ አስተዋጽኦ አድርገዋል:: ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በሶሻል ሳይንስ ኮሌጅ የፖለቲካ ሳይንስና ዓለማአቀፍ ግንኙነት (Political Science and International Relations) ትምህርት ክፍል መምህር ሆነው በማገልገል ላይ ይገኛሉ፡፡
Good job ARTS. Yet who is Prof Getachew Assefa? Don’t you have his bio?
ያቀረባችሁት ዜና የተሟላ አይደለም። ከፕሮፌሰር መረራ ጉዲና ሌላ አምስቱ እነማናቸው? 1/ፕሮፌሰር ሂሩት ወልደማርያም፣ 2/ፕሮፌሰር ተፈሪ ገድፍ፣ 3/ፕሮፌሰር ምሩፅ ግደይ፣ 4/ፕሮፌሰር ሃጎስ አሸናፊ፣ 5/ ፕሮፌሰር ጌታቸው አሰፋ ናቸው። ፕሮፌሰር መረራ ሳይጨመሩበት ምን እንደሚመስል ግልጽ ነው! ከኣመት በፊት ፕሮፌሰር ጣሰው ወ/ሃና ካሕሳይ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት ሆነው በትምህርት ሚኒስቴር መሾማቸውን እናስታውሳለን። ፋና የዘገበው፣ ምርጫው የተደረገው በዩኒቨርሲቲው ቦርድ፣ በመምህራን፣ በተማሪዎች እና በኢንዱስትሪ አካላት ተሣትፎ እንደ ነበረ ነው። ተማሪዎቹ እነ ማናቸው? ከኢንዱስትሪ ግለ ሰቦችስ? ከመምህራን እነ ማን ተሳተፉ? የህወሓት ተጽእኖ አሁን ስለ ተወገደ ይኸ መጣራት አለበት፡፡ በነገራችን ላይ፣ እነዚህ ሙሉ ፕሮፌሰርነት ማእረግ የተሰጣቸው የዲፓርትመንት መሪ የሚሆኑት፣ ለምርምር የሚሰጡ እርዳታዎችን የሚያስተባብሩና የሚመድቡ፣ የምርምሮችን አቅጣጫ የሚተልሙ ናቸው። ድህረ ምሩቃን በሚያደርጉት ጥናት ላይ በዋናነት ኮሚቴ ላይ የሚሰየሙት እነ ቆስጠንጢኖስ በርሀ ናቸው። በሌላ አነጋገር፣ ጥናቶች የህወሓትን ፖለቲካ ኣላማ ለማስፈጸም ውለዋል።