ከንቲባ ታከለ ኡማ የዲጂታል መታወቂያ መሠጠት ከተጀመረባቸው ወረዳዎች በአንዱ የድንገቴ ጉብኝት አደረጉ ፡፡
የነዋሪነት መታወቂያን በዲጂታል ለመቀየር በታቀደው መሠረት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በአዲስከተማ ክ/ከተማ የዲጂታል መታወቂያን ለነዋሪዎች መስጠት መጀመሩ ይታወቃል፡፡
ከንቲባዉም በዚሁ ክፍለከተማ የዲጂታል መታወቂያ መሠጠት በጀመረበት አንድ ወረዳ ምልከታ አድርገዋል፡፡
በጉብኝታቸውም ላይ ከተገልጋዮች ፣ ከባለሞያዎች እና የወረዳው አመራሮች ጋር መነጋገራቸዉን ከከንቲባዉ ጽ/ቤት ያገኘነዉ መረጃ ያመለክታል፡፡