Politics

ጀርመን የአውሮፓ ኩባንያዎችን እየተቃወመች ነው፡፡

ጀርመን የአውሮፓ ኩባንያዎችን እየተቃወመች ነው፡፡

የአውሮፓ ሚሳኤል አምራች ኩባንያዎች ለሳውዲ አረቢያ የጦር መሳሪያ እንዳይሸጡላት ጀርመን ጫና እያሳደረች ነው፡፡

ጀርመን ሪያድ ከአውሮፓ ኩባንያዎች የመሳሪያ ግዥ እንዳትፈፅም የፈለገችበትን ምክንያት  ሀገሪቱ ከተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች ጋር በየመን የምታካሂደውን  ዘመቻ ስለማትደግፍ ነው፡፡

ኩባንያዎቹ ለሳውዲ በራዳር የሚመራ እና ከእይታ ውጭ የሆነ ተወንጫፊ ሚሳኤል  እንዳይሸጡ የጀርመን ተቃውሞ እንግሊዝን እና ፈረንሳይን ቅር አሰኝቷል ነው የተባለው፡፡

ጀርመን የጀመረችው እንቅስቃሴ አዲስ ፖለቲካ ጥያቄን አስነስቷል፡፡ ይህም ከፈረንሳይ ጋር በመሆን ይህን ሚሳኤል የሚያመርቱ ኩባንያዎች ለይ ጥብቅ የሆነ እምጃ እንዲወሰድ የሚል ነው፡፡

ሳውዲ አረቢያ እንደ በፈረንጆቹ አቆጣጠር በ2014 ተምዘግዛጊ ሚሳኤሎችን እና የውጊያ አውሮፕላኖችን ለመግዛት ከአውሮፓ ኩባንያዎች ጋር የ1 ቢሊዮን ዶላር ስምምነት መፈራረሟ ይታወሳል፡፡

 

መንገሻ ዓለሙ

Related Articles

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Back to top button