COVID-19

ህብረተሰቡ ሁለተኛውን ዙር የኮቪድ 19 መከላከያ ክትባት ወደ ክትባት መስጫ ጣቢያዎች በመቅረብ እንዲከተብ ጥሪ ቀረበ

የሁለተኛዉ ዙር የኮቪድ 19 መከላከያ ክትባት ዘመቻ እድሚያቸው 12 አመትና ከዚያ በላይ ለሆኑ ሁሉ በመንግስት ጤና ተቋማትና በጊዚያዊ ክትባት መስጫ ጣቢያዎች ከየካቲት 7 እስከ 16/2014 ዓ.ም መስጠት ተጀምሯል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ ሃላፊ ዶር ዮሃንስ ጫላ በሰጡት መግለጫ እንዳሳዎቁት፤
እስካሁን ሰባት ሺህ 426 በላይ የሚሆኑ ሰዎች በወረርሽኙ ህይወታቸው አልፏል።


ክትባቱን ተደራሽ ከማድረግ አንጻርም፤ እስካሁን አንድ ነጥብ አንድ ሚሊዬን ሰዎች አንድ ጊዜ፤ 700 ሺህ የሚሆኑት ደግሞ ሁለት ጊዜ ተከትበዋል ብለዋል። ይህ ወቅት የቫይርሱ 4ኛ ዙር ማእበል የተነሳበት በመሆኑ ህብረተሰቡ በመከተብና ሌሎችን በማስከተብ ወረርሽኙን እንዲግታ ጥሪ አቅርበዋል። በዚህ በሁለተኛው ዙር ዘመቻ ለግማሽ ሚሊዮን ሰዎች ክትባት ለመስጠት ግብ መቀመጡን በመግልጫው ተጠቅሷል።

Related Articles

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Back to top button