World News

በደቡባዊ ምስራቅ የህንድ ግዛቶች የተከሰተው አውሎ ንፋስ በርካታ ነዋሪዎችን ስጋት ላይ ጥሏል::

አዲስ አበባ፣ ህዳር 16፣ 2013 በደቡባዊ ምስራቅ የህንድ ግዛቶች የተከሰተው አውሎ ንፋስ በርካታ ነዋሪዎችን ስጋት ላይ ጥሏል:: ሳይክሎን ኒቫር በመባል የሚታወቀው አውሎ ንፋስ በደቡብ ምስራቅ ህንድ በሚገኙ ሶስት ግዛቶች በፍጥነት እየገሰገሰ መሆኑን ተከትሎ ሰዎች ከቤታቸው እንዳይወጡ ትእዛዝ ተላልፎላቸዋል፡፡

ሰዎች በአደባባይ እንዳይሰባሰቡና ተጨማሪ መመሪያዎች እስኪተላለፉላቸው ድረስ በጥንቃቄ እንዲቆዩ የአካባቢው ባለስልጣናት አስጠንቅቀዋል ነው የተባለው፡፡ አደጋው ሊያደርስ የሚችልውን ጉዳት መከላከል ሲባልም መንግስት ከ1 ሺህ በላይ የነፍስ አድን ሰራተኞችን በስፍራው አሰማርቷል፡፡

አልጀዚራ እንደዘገበው አየአውሎ ንፋስ አደጋው የተጋረጠባቸው ታሚልናዱ፣ ፓዱቸሪና አንድራ የተባሉ የህንድ ግዛቶች ናቸው፡፡ የሀገሪቱ የአየር ትንበያ ተቋም አውሎ ንፋሱ በነዚህ ግዛቶች በቀጣዮቹ ቀናት ከፍተኛ ጉዳት ሊያደርስ እንደሚችል ትንበያውን ተናግሯል፡፡ በትንበያው መሰረት አውሎ ንፋሱ ከባድ ዝናብ እንደሚያስከትልና በሰዓት እስከ 145 ኪሎ ሜትር ፍጥነት ሊኖረው ስለሚችል አደገኝነቱ እንደሚያይል ይጠበቃል፡፡ ህንድ በቅርቡ በከባድ አውሎ ንፋስ ተመትታ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች መሞታቸውና በርካታ ንብረት መውደሙ የሚታወስ ነው፡፡

Show More

Related Articles

One Comment

  1. Western Art and the Wider World explores the evolving relationship between the Western canon of art, as it has developed since the Renaissance, and the art and culture of the Islamic world, the Far East, Australasia, Africa and the Americas. Explores the origins, influences, and evolving relationship between the Western canon of art as it has developed since the Renaissance and the art and culture of the Islamic world, the Far East, Australasia, Africa and the Americas Makes the case for world art long before the fashion of globalization Charts connections between areas of study in art that long were considered in isolation, such as the Renaissance encounter with the Ottoman Empire, the influence of Japanese art on the h-century French avant-garde and of African art on early modernism, as well as debates about the relation of contemporary art to the past. Written by a well-known art historian and co-editor of the landmark Art in Theory volumes

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Back to top button