Africa

ኤርትራ ልክ እንደ ጎረቤቷ ኢትዮጵያ ዜጎቿን ወደ ቤታችሁ ተመለሱ እያለች ነው፡፡

ኒውስ አፍሪካ እንደዘገበው የኤርትራው የውጨ ጉዳይ ሚኒስትር ኡስማን ሳልህ ከዶቸዌሌ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኤርትራዊያን ወደ ሀገራቸው ገብተው መኖር ይችላሉ ብለዋል፡፡
ውጭ ጉዳይ ሚንስትሩ እንዳሉት በየትኛውም ምክንያት ከሀገሩ የወጣ ማንኛውም ኤርትራዊ ዜጋ ከእንግዲህ በፈለገው ጊዜ ወደ ሀገሩ ተመልሶ የመኖርና የመስራት ነጻነቱን የሚጋፋው አካል የለም፡፡
ከኢትዮጵያ ጋር ለዓመታት ሰላምም ጦርነትም የለም ስትባባል የቆየችው ኤርትራ በቅርቡ ከኢትዮጵያና ከሌሎች የምስራቅ አፍሪካ ሀገሮች ጋር ሰላማዊ ግንኙነቶችን መጀመሯ ይታወሳል፡፡ 
አሁን ደግሞ በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ዜጎቿን በሰላም ወደ እናት ሀገራችሁ ግቡ የሚል መልእክት አስተላልፋለች፡፡

አርትስ 24/12/2010

Related Articles

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Back to top button