loading
ሞሮኮ በማረሚያ ቤቶቿ ባደረገችው ምርመራ ከ300 በላይ ታራሚዎች በኮቪድ 19 መያዛቸውን አረጋገጠች::

አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 21 ፣ 2012 ሞሮኮ በማረሚያ ቤቶቿ ባደረገችው ምርመራ ከ300 በላይ ታራሚዎች በኮቪድ 19 መያዛቸውን አረጋገጠች:: ይሄ ቁጥር የተገኘው በሶስት እስር ቤቶች በሚገኙ 1 ሺህ 736 እስረኞች ላይ በተደረገ ምርመራ መሆኑን አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ በዘገባው አስነብቧል፡፡ከነዚህ ሶስት እስር ቤቶች መካከል ደግሞ 303 በኮሮና ቫይረስ የተያዙት ሰዎች የተገኙት በሀገሪቱ ደቡባዊ ክፍል በሚገኝ ኦዋራዛቴ […]

በማሊ የሥደተኞች ጣቢያ በእሳት በመውደሙ ዜጎች ለሁለተኛ ስደት ተጋልጠዋል::

አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 21 ፣ 2012 በማሊ የሥደተኞች ጣቢያ በእሳት በመውደሙ ዜጎች ለሁለተኛ ስደት ተጋልጠዋል:: በማሊ በተከሰተው የርስበበርስ ግጭት ምክንያት መኖሪያ ቀያቸውን ለቀው በጊዜያዊ መጠለያ የነበሩ ሰዎች መኖሪያቸው ሙሉ በሙሉ መውደሙ ተሰምቷል፡፡አሶሼትድ ፕሬስ እንደዘገበው በዚህ ጊዜያዊ መጠለያ ጣቢያ ውስጥ እስከ ሁለት ዓመት የቆዩ ከ1 ሺህ በላይ የሚሆኑ ማሊያዊያን ስደተኞች ይኖሩ ነበር፡፡ ስደተኞቹ እንደተናገሩት አለን […]

ምክር ቤቱ ምርጫ ቦርድ ጠቅላላ ምርጫን በተመለከተ ያቀረበውን የውሳኔ ሀሳብ ለዝርዝር እይታ ለቋሚ ኮሚቴ መራ::

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 22፣ 2012 ምክር ቤቱ ምርጫ ቦርድ ጠቅላላ ምርጫን በተመለከተ ያቀረበውን የውሳኔ ሀሳብ ለዝርዝር እይታ ለቋሚ ኮሚቴ መራ የኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የመሰብሰቢያ አደራሽ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባውም የተለያዩ ውሳኔዎችን መርምሮ አጽድቋል።ምክር ቤቱ በመደበኛ ስብሰባው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጠቅላላ ምርጫን በተመለከተ ያቀረበውን የውሳኔ ሐሳብን ተመልክቷል።የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ […]

ኢትዮጵያ ተ.መ.ድ ኮቪድ-19ን ለመግታት የጀመረውን ኢኒሺየቲቭ እንደምትደግፍ  ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ገለጹ::

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 22፣ 2012 ኢትዮጵያ ተ.መ.ድ ኮቪድ-19ን ለመግታት የጀመረውን ኢኒሺየቲቭ እንደምትደግፍ  ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ገለጹ:: የተባበሩት መንግስታት ባለአደራ ፈንድ ለኮቪድ 19 ምላሽ ለመስጠት የጀመረውን “Rise for All” ኢኒሺየቲቭ ኢትዮጵያ መቀላቀሏን ፕሬዚዳንቷ ትናንት አስታውቀዋል።በተመድ ምክትል ዋና ጸሃፊ አሚና መሃመድ ይፋ የሆነው ፕሮጀክት የዓለም ሴት መሪዎች ወረርሽኙ ያስከተለውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳት ለመግታት የሚረዳ መፍትሄ ለማበጀት ህብረታቸውን፣ ጥረታቸውንና ሃብታቸውን በማቀናጀትና በማንቀሳቀስ እንዲሰሩ ጥሪ አቅርቧል።ከፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ በተጨማሪ የኖርዌይ ጠቅላይ ሚኒስትር ኢርና ሶልበርግና የባርባዶስ አቻቸው ሚያ ሞትሊ የተ.መ.ድ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተሮች ፕሮጀክቱን ለመደገፍ  የሚያግዝ የቪዲዮ ውይይት አድርገዋል። “ኮቪድ19 ዓለም አቀፍ ቀውስ መሆኑን ተከትሎ ምላሽ ለመስጠት መዘግየት ሞትን መጥት ነው፤ ሁላችንም ተመሳሳይ ጠላትን የተጋፈጥን በመሆናችን ሰብዓዊ አቅማችንን አንድ ላይ በማስተባበር ለውጤት መሰለፍ አለብን” ብለዋል ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ። “ቫይረሱን በተናጠል ወይም በአንድ አገር ጥረት ብቻ መግታት ስለማይቻል ተመድ ጋራ ትብብር ያቀረበውን ጥሪ እደግፋለሁ” ብለዋል።  የፈንዱ ግብ በመጀመሪያዎቹ ዘጠኝ ወራት 1 ቢሊዮን ዶላር ማሰባሰብ ሲሆን በሁለት አመታት ውስጥ ደግሞ ሁለት ቢሊዮን ዶላር ለማሰባሰብ ያለመ ነው።በዚህም ዝቅተኛና መካከለኛ ገቢ ያላቸውን አገሮች፣ ህፃናትን፣ ሴቶችንና ለአደጋ የተጋለጡ  የማህበረሰብ ክፍሎችን ለመደገፍ አቅጣጫ ተይዟል።

ሚኒስቴሩ በሃብት ማሰባሰብ ስትራቴጂ ካሰባሰበዉ ሀብት ዉስጥ 15 ሚሊዮን ብሩን ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸዉ ተቋማት አስረከበ፡፡

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 22፣ 2012 ሚኒስቴሩ በሃብት ማሰባሰብ ስትራቴጂ ካሰባሰበዉ ሀብት ዉስጥ 15 ሚሊዮን ብሩን ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸዉ ተቋማት አስረከበ፡፡የሴቶች፣ ህፃናትና ወጣቶች ሚኒስቴር ለአርትስ በላከዉ መግለጫ እንዳስታወቀዉ፤ ሚኒስቴሩ ባካሄደዉ የርክክብ ስነስርዓት ላይ የተገኙት የወጣቶች ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ ወ/ሮ ህይወት ኃይሉ ባስተላለፉት መልዕክት ቫይረሱ በፍጥነት የሚዛመት በመሆኑ የቆየንበት  የመጠጋጋት፣ የመጨባበጥና የመሳሳም ልማድን መተዉ አለብን ብለዋል፡፡ ሚኒስትር ዲኤታዋ […]