loading
ጠቅላይ ሚኒስትር ቤናሚን ኔታኒያሁ ለፍልስጤማዊው ወጣት ሞት ይቅርታ ጠየቁ ::

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 1 ፣ 2012 ጠቅላይ ሚኒስትር ቤናሚን ኔታኒያሁ ለፍልስጤማዊው ወጣት ሞት ይቅርታ ጠየቁ :: የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤናሚን ኔታያሁ ለወጣቱ እናት የይቅርታ መልእክታቸውን ያተላለፉት ከተገደለ አንድ ሳምንት ካለፈው በኋላ ነው፡፡ እየሩሳሌም ውስጥ በእስራኤል ፖሊሶች የተገደለው የ32 ዓመቱ ወጣት ኢያድ ሀላክ ከልጅነቱ ጀምሮ የኦቲዝም ታማሚ ነበር ተብሏል፡፡ ሚድል ኢስት ሞኒተር እንደዘገበው ኔታኒያሁ በሰጡት መግለጫ […]

ኒው ዚላንድ አዲስ የኮሮናቫይረስ አለማስመዝገቧን ተከትሎ ክልከላዎችን በሙሉ ልታነሳ ነው ::

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 1 ፣ 2012 ኒው ዚላንድ አዲስ የኮሮናቫይረስ አለማስመዝገቧን ተከትሎ ክልከላዎችን በሙሉ ልታነሳ ነው ::የኒው ዚላንዷ ጠቅላይ ሚኒስትር ጀሲንዳ አርደን በሀገራቸው ቫይረሱ ያለባቸው ሰዎች እንዴሌሉ ተናግረው ከእንግዲህ አካላዊ መራራቅን እንጅ እንቅስቃሴን አንገድብም ብለዋል፡፡ ይሁን እንጅ ከውጭ የሚገቡ ዜጎቻችን ለ14 ቀናት በለይቶ ማቆያ እንዲቀመጡ ማድረግ የግድ ይላል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሯ ለተገኘው ውጤት ሁሉንም ዜጎቻቸውን […]

ግብፅ በኮሮናቫይረስ ምክንያት 47 ዶክተሮቿን በሞት ማጣቷ ትልቅ ስጋት ሆኖባታል ተባለ::

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 2 ፣ 2012 ግብፅ በኮሮናቫይረስ ምክንያት 47 ዶክተሮቿን በሞት ማጣቷ ትልቅ ስጋት ሆኖባታል ተባለ::የብግብፅ የህክምና ማህበር በሰጠው መግለጫ የሀገሪቱ የጤና አጠባበቅ ስርዓት በፍጥነት ካልተስተካከለና ለሀኪሞች ልዩ እንክብካቤ ካልተደረገላቸው የበለጠ አደጋ ሊደርስ እንደሚችል አስጠንቅቋል፡፡ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ብቻ በኮሮናቫይረስ ሳቢያ ሰባት ዶክተሮች መሞታቸው ሁኔታው ምን ያህል አደገኛ እየሆነ መምጣቱን ያሳያል ነው የተባለው፡፡ ከሁለት […]

ኬንያዊያን ፖሊስ በንፁሀን ዜጎች ላይ የሚፈፅመውን ግድያ ያቁም የሚል ተቃውሞ እያሰሙ ነው::

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 2 ፣ 2012 ኬንያዊያን ፖሊስ በንፁሀን ዜጎች ላይ የሚፈፅመውን ግድያ ያቁም የሚል ተቃውሞ እያሰሙ ነው:: በኬንያ የኮሮናቫይረስ ስርጭትን ለመግታት የተጣለውን የእንቅስቃሴ እገዳ ተከትሎ ፖሊስ ህግ በማስከበር ሰበብ በርካታ የሰብዓዊ መብቶችን እየጣሰ እንደሆነ ለተቃውሞ አደባባይ የወጡ ሰዎች ተናግረዋል፡፡ አልጀዚራ እንደዘገበው መንግስት እገዳውን ከጣለ ጀምሮ በተለያዩ ጊዜያት በፖሊስና በነዋሪዎች መካከል በተከሰቱ ግጭቶች ከ15 ያላነሱ […]

የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የሶስትዮሽ ድርድር ድርድረ በሚኒስትሮች ደረጃ ተካሄደ፡፡

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 3 ፣ 2012 የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የሶስትዮሽ ድርድር ድርድረ በሚኒስትሮች ደረጃ ተካሄደ፡፡ዉሃ መስኖና እና ኢነርጂ ሚኒስቴር እንዳስታወቀዉ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የሶስትዮሽ ድርድር በበይነ-መረብ የቪዲዮ ኮንፈረንስ ታዛቢዎች በተገኙበት በውሃ ጉዳይ ሚኒስትሮች ደረጃ ተካሂዷል የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን የሙሌት እና ዓመታዊ የውሃ አለቃቅ በተመለከተ በኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብጽ መካከል የሚደረገው የሶስትዮሽ ድርድር […]

የብሩንዲው ፕሬዚዳንት ፒዬር ንኩሩንዚዛ በልብ ህመም በድገንገት ህይዎታቸው አለፈ ::

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 3 ፣ 2012የብሩንዲው ፕሬዚዳንት ፒዬር ንኩሩንዚዛ በልብ ህመም በድገንገት ህይዎታቸው አለፈ ::የብሩንዲ መንግስት ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው ፕሬዚዳንቱ በልብ ህመም መሞታቸው ተረጋግጧል፡፡ አልጀዚራ እንደዘገበው ፕሬዚዳንቱ ባለፈው ቅዳሜ በአንድ የቮሊቦል ጨዋታ ውድድር ላይ ታድመው የነበረ ሲሆን በዚያው ምሽት ታመው ወደ ሆስፒታል ተወስደዋል፡፡ ሆስፒታል ከገቡ በኋላ የጤናቸው ሁኔታ መሻሻል አሳይቶ የነበረ ቢሆንም ሰኞ እለት በተደረገላቸው […]

በሰሜን ምሥራቅ ናይጄሪያ ጽንፈኛ ጂሃዲስቶች ሳይፈጽሙት አልቀረም በተባለ ጥቃት በትንሹ 59 ሰዎች ተገደሉ።

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 3 ፣ 2012 በሰሜን ምሥራቅ ናይጄሪያ ጽንፈኛ ጂሃዲስቶች ሳይፈጽሙት አልቀረም በተባለ ጥቃት በትንሹ 59 ሰዎች ተገደሉ።የጂሃዲስት ታጣቂ ቡድን በሰሜናዊ ናይጄሪያ ባደረሰው ጥቃት በትንሹ 59 ንጹሃን ዜጎች ተገድለዋል፡፡ በቦርኖ ግዛት ስር በምትገኝ ጉቢዮ በምትባል የገጠር መንደር ታጣቂዎች በፈፀሙት ጥቃት በርካታ ንጹሃን ዜጎችን መግደላቸውን ነው የቢቢሲ ዘገባ የሚያስረዳው፡፡ ጥቃቱ የተፈጸመባት መንደር ሙሉ ለሙሉ ውድመት […]

የኮሮና ቫይረስ  በ164 ሰዎች ላይ ሲገኝባቸው፤ የ5 ሰዎች ህይወት አልፏል

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 4፣ 2012  የኮሮና ቫይረስ  በ164 ሰዎች ላይ ሲገኝባቸው፤ የ5 ሰዎች ህይወት አልፏል፡፡ ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 6 ሺህ 630 የላብራቶሪ ምርመራ 190 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 2 ሺህ 670 መድረሱንም የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ ዛሬ ባወጡት ሪፖርት አመላክተዋል። ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው […]

ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ የኢትዮጵያ ሕዝብ ለአረንጓዴ ልማት እንዲነሳ ጥሪ አስተላለፉ::

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 4፣ 2012 ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ የኢትዮጵያ ሕዝብ ለአረንጓዴ ልማት እንዲነሳ ጥሪ አስተላለፉ:: የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዓቢይ አህመድ አሻራችንን በማኖር ለኢትዮጵያ አረንጓዴ ምንጣፍ እንዘርጋ በማለት ጥሪ አቀረቡ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ በማህበራዊ ትስስር ገጾቻቸው ባስተላለፉት መልዕክት የአረንጓዴ ልማት ጥቅም በመረዳት መሥራት ያስፈልጋል። አረንጓዴ ዐሻራ ከሥነ ውበት በላይ ነው። የምንተነፍሰው አየር ነው። የምንጠቀመው እንጨት […]

በኢትዮጵያ የሰብዓዊ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው ሰዎች ቁጥር ወደ 16 ሚሊየን ከፍ አለ::

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 4፣ 2012 በኢትዮጵያ የሰብዓዊ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው ሰዎች ቁጥር ወደ 16 ሚሊየን ከፍ አለ::በኮሮና ቫይረስ ምክንያት በኢትዮጵያ የሰብዓዊ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው ሰዎች ቁጥር ወደ 16 ነጥብ 5 ሚሊየን ከፍ ማለቱን በኢትዮጵያ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ፅህፈት ቤት አስታወቀ።  የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ከኢትዮጵያ መንግስት እና ከሌሎች አጋር አካላት ጋር በመተባበር የ2020 የሰብዓዊት እርዳታ ፍላጎቶች ላይ ክለሳ […]