loading
የዋጋ ንረት ለማረጋጋት ከውጭ የሚገቡ ሸቀጦች ለህብረተሰቡ መድረሳቸውን የሚያረጋግጥ ጠንካራ የቁጥጥር ስርአት መዘርጋት እንደሚገባ ምክር ቤቱ አሳሰበ።

የዋጋ ንረት ለማረጋጋት ከውጭ የሚገቡ ሸቀጦች ለህብረተሰቡ መድረሳቸውን የሚያረጋግጥ ጠንካራ የቁጥጥር ስርአት መዘርጋት እንደሚገባ ምክር ቤቱ አሳሰበ። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 5ኛ መደበኛ ስብሰባ የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴርን የ8 ወራት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ሲገመግም በኑሮ ውድናትና ህገ-ወጥነት ላይ ትኩረት አድርጎ ተወያይቷል። ሚኒስትሩ አቶ ገብረመስቀል ጫላ በወጪ ንግድ ገቢ፣ የመሰረታዊ ፍጆታ እቃዎች አቅርቦትና ስርጭት፣ እንዲሁም የአሰራር […]

የመስኖ ዘርፍ ቴክኖሎጂ ለማሳደግ እና ክህሎት ያለው የሰው ሀይል ለማፍራት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ፡፡

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 28፣ 2014 የመስኖ ዘርፍ ቴክኖሎጂ ለማሳደግ እና ክህሎት ያለው የሰው ሀይል ለማፍራት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ፡፡ ስምምነቱ የተፈረመው በመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መካከል ነው፡፡ ይህ ስምምነት የተናበበና የተቀናጀ የአሠራር ሥዓርት በመዘርጋት የሀብትና የጊዜ ብክነትን በማስቀረት ብቁ የሰው ኃይል በማፍራት በመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር በሚተገበሩ ፕሮግራሞች ላይ እንዲሳተፉ ያግዛል ነው የተባለው፡፡ […]

የዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት አቃቤ ህግ በዳርፉር ያለውን የክስ ሁኔታ መቋጫ ማበጀት እፈልጋለሁ አሉ፡፡

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 28፣ 2014 የዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት አቃቤ ህግ በዳርፉር ያለውን የክስ ሁኔታ መቋጫ ማበጀት እፈልጋለሁ አሉ፡፡የፍርድ ቤቱ ዋና አቃቤ ህግ ካሪም ካህን በሄግ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ የቀድሞው የሱዳን ፕሬዚዳንት ኦማር አልበሽር በቅርቡ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ ወይ ተብለው ሲጠየቁ በዳርፉር ያለውን ሁኔታ መዝጋት እንደሚፈልጉ ተናግረዋል ተብሏል። የቀድሞ የሱዳን ሚሊሻ ሃላፊ አሊ […]

የዋጋ ጭማሬ የታየበት የበዓል ግብይት

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 13፣ 2014 የዘንድሮው የበዓል ግብይት በሁሉም መልኩ የዋጋ ጭማሬ የታየበት መሆኑን ሸማቾች ተናገሩ። የፋሲካ በዓልን በማስመልከት በተለያዩ አካባቢዎች በተዘጋጁ ኤግዚቢሽኖች፣ የበሬ፣ የበግና ፍየል፣ የዶሮ ግብይት ስፍራዎች የዋጋ ንረት ታይቷል፡፡ ለአብነትም የበሬ ዋጋ ከባለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር ከ10 እስከ 15 ሺህ ብር ጭማሪ ማሳየቱ ነው የተገለፀው፡፡  ለበሬ ዋጋ መጨመር በማጓጓዝ ሂደት የነዳጅ ዋጋ […]

ኤች አር 6600” እና “ኤስ 3199” ረቂቅ ሕጎችን የሚቃወም ሰልፍ በኒው ጀርሲ ግዛት ተካሄደ::

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 13፣ 2014 ኤች አር 6600” እና “ኤስ 3199” ረቂቅ ሕጎችን የሚቃወም ሰልፍ በኒው ጀርሲ ግዛት ተካሄደ:: በትናትናው ዕለት በ “ኤስ 3199” ረቂቅ ሕግ አርቃቂ ሴናተር ሮበርት ሜኔንዴዝ (ኒው ጀርሲ) ቢሮ ፊት ለፊት በተከናወነው ሰልፍ ላይ “ረቂቅ ሕጎቹ ኢትዮጵያንና ኤርትራን የሚጎዱ ናቸው”፣ ”ማዕቀብ ይገድላል ማዕቀብ ምንም አይጠቅምም”፣ “ኤች አር 6600” እና “ኤስ 3199” […]

የእስራኤል ተዋጊ ጄቶች በጋዛ ላይ ጥቃት መሰንዘራቸው ተነገረ፡፡

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 13፣ 2014 የእስራኤል ተዋጊ ጄቶች በጋዛ ላይ ጥቃት መሰንዘራቸው ተነገረ፡፡ እስራኤል በዚህ ሳምንት ለሁለተኛ ጊዜ በማእከላዊ ጋዛ ሰርጥ የአየር ጥቃት መፈፀሟ ተነግሯል፡፡ አልጄዚራ የዐይን እማኞችን ጠቅሶ እንደዘገበው የእስራኤል ተዋጊ ጄቶች የሮኬት ሞተሮችን ከሚያመርተው እና ከመሬት በታች በሚገኘው ህንፃ ላይ ጥቃት አድርሰዋል። የመረጃ ምንጩ ይሄንን ዘገባ እስካጠናቀረበት ሰዓት ድረስ በጥቃቶቹ በማዕከላዊ ጋዛ በሚገኘው […]

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለጎዳና ተዳዳሪዎችና አቅመ ደካሞች በቤተ-መንግሥት ማዕድ አጋሩ::

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 17፣ 2014 ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለጎዳና ተዳዳሪዎችና አቅመ ደካሞች በቤተ-መንግሥት ማዕድ አጋሩ:: ጠቅላይ ሚኒስትሩ የትንሳኤን በዓል ምክንያት በማድረግ ጧሪ ለሌላቸው አረጋዊያን፣ የጎዳና ተዳዳሪዎች፣ በተለያዩ ምክንያቶች ቤተሰቦቻቸውን ላጡ ህፃናትና ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው በድምሩ 230 ወገኖች ማዕድ አጋርተዋል።በመርሃ-ግብሩ ላይ የተገኙት ወገኖች በቤተ-መንግሥት ተገኝተን በጠቅላይ ሚኒስትሩ ለተደረገልን ግብዣና መልካም መስተንግዶ እናመሰግናለን ብለዋል። ማዕድ ተጋሪዎቹ […]

የጥቁር አንበሳ የልብ ሕክምና ማዕከል የማስፋፊያ ፕሮጀክት የመጀመሪያ ምዕራፍ ተጠናቆ ሥራ ጀመረ፡፡

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 17፣ 2014 የጥቁር አንበሳ የልብ ሕክምና ማዕከል የማስፋፊያ ፕሮጀክት የመጀመሪያ ምዕራፍ ተጠናቆ ሥራ ጀመረ፡፡ በዛሬው ዕለት የተመረቀው የፕሮጀክቱ የመጀመሪያ ምዕራፍ የተለያዩ የሕክምና ግብዓቶች እንደተሟሉለት ተነግሯል። ለአብነትም በአፍሪካ ብቸኛው ልብ ሳይከፈት ቀዶ ህክምና ማድረግ የሚያስችል መሣሪያ ተበርክቶለታል ተብሏል፡፡ በአጠቃላይ ለፕሮጀክቱ 39 ነጥብ 720 ሚሊየን ዶላር ወጪ የሚደረግበት ሲሆን ወጪውም 50 በመቶው በኔዘርላንድስ መንግሥት […]

ትምህርት ሚኒስቴር የ2013 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል የዩኒቨርሲቲ ምደባን ይፋ አደረገ።

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 17፣ 2014 ትምህርት ሚኒስቴር የ2013 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል የዩኒቨርሲቲ ምደባን ይፋ አደረገ። የ2013 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስደው ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች በወጪ መጋራት የመግቢያ መቁረጫ ነጥብ ላመጡ ተማሪዎችምደባ ማድረጉን ሚኒስቴሩ ገልጿል። ከዚህ በፊት በተገለጸዉ የመቁረጫ ነጥብ ከኦሮሚያ፣ አማራ፣ አፋርና ቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች ተጨማሪ ተማሪዎች ምደባ […]

ተሸከርካሪን በመጠቀም የሚፈፀም የቅሚያ ወንጀል ‹‹ሿሿ›› መበራከት

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 18፣ 2014 በአዲስ አበባ የሌብነት ወንጀል በየጊዜው እየጨመረ መምጣቱን ፖሊስ አስታወቀ:: በአዲስ አበባ ለህዝብ ስጋት ከሆኑ ከባድ ወንጀሎች መካከል በተለያየ መንገድ የሚፈፀም የሌብነት ወንጀል በየጊዜው እየጨመረ መምጣቱን የአዲስ አበባ ፖሊስ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ኮማንደር ፋሲካ ፋንታ ተናግረዋል። ከእነዚህ ከባድ ወንጀሎች ውስጥ ተሸከርካሪ በመጠቀም የሚፈፀም የቅሚያ ወንጀል፣ በተለምዶ ‹‹ሿሿ›› የሚባለው መኪና ውስጥ የሚፈፀም […]