loading
በጋምቤላ ክልል በአራት ወረዳዎች በደረሰ የጎርፍ አደጋ ከ4 ሺህ በላይ ሰዎች ከመኖሪያቸው መፈናቀላቸውን የክልሉ አደጋ ስጋት አመራር አገልግሎት አስታወቀ።

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 16፣ 2014 በጋምቤላ ክልል በአራት ወረዳዎች በደረሰ የጎርፍ አደጋ ከ4 ሺህ በላይ ሰዎች ከመኖሪያቸው መፈናቀላቸውን የክልሉ አደጋ ስጋት አመራር አገልግሎት አስታወቀ።የጎርፍ አደጋው የተከሰተው በክልሉ ደጋማው አካባቢ ሲሆን የአደጋው ተጠቂዎች በላሬ፣ መኮይ ዋንቱዋ እና ኢታንግ በተባሉ ልዩ ወረዳዎች የሚገኙ ቀበሌዎች መሆናቸው ተነግሯል፡፡ የክልሉ አደጋ ስጋት አመራር አገልግሎት ኃላፊ አቶ ጋትቤል ሙን በጎርፍ አደጋው […]

የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ለአቅመ ደካሞችና ለጎዳና ተዳዳሪዎች ለአንድ ሳምንት የሚቆይ ነፃ የህክምና አገልግሎት መስጠት ጀመረ፡፡

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 16፣ 2014 የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ለአቅመ ደካሞችና ለጎዳና ተዳዳሪዎች ለአንድ ሳምንት የሚቆይ ነፃ የህክምና አገልግሎት መስጠት ጀመረ፡፡ቢሮው ለአንድ ሳምንት በሚቆየው ነፃ የምርመራ እና የህክምና አገልግሎት 17 ሺህ ያህል የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ተጠቃሚ እንደሚሆኑ አስታውቋል። የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዮሐንስ ጫላ በዘውዲቱ መታሰቢያ ሆስፒታል በመገኘት አገልግሎቱን ባስጀመሩበት ወቅት ህብረተሰቡ በተለያዩ […]

የምዕራባውያኑ ሀገራት መሪዎች በኢራን የኒውክሌር ስምምነት ላይ መወያየታቸው ተሰማ።

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 16፣ 2014 የምዕራባውያኑ ሀገራት መሪዎች በኢራን የኒውክሌር ስምምነት ላይ መወያየታቸው ተሰማ። የአሜሪካ፣ የእንግሊዝ፣ የፈረንሳይ እና የጀርመን መሪዎች የ2015ቱ የኢራን የኒውክሌር ስምምነትን ለማደስ በሚደረገው ጥረት ዙሪያ ውይይት ማድረጋቸውን ዋይት ሀውስ እሁድ እለት አስታውቋል።በዚሁ መግለጫ ሀገራቱ በኢራን የኒውክሌር መርሃ ግብር ላይ በመካሄድ ላይ ባለው ድርድር፣ በመካከለኛው ምስራቅ አካባቢ ያሉ አጋሮችን ድጋፍ ማጠናከር እና የኢራንን […]