loading
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ዲና ሙፍቲ በሳምንታዊ መግለጫቸው በአበይት ፖለቲካዊ፣ ምጣኔ ሀብታዊ እና የዜጋ ዲፕሎማሲ ክንውኖችን ዙሪያ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

አዲስ አበባ ፣ ሃምሌ 2፣ 2013  የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ዲና ሙፍቲ በሳምንታዊ መግለጫቸው በአበይት ፖለቲካዊ፣ ምጣኔ ሀብታዊ እና የዜጋ ዲፕሎማሲ ክንውኖችን ዙሪያ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡ ትናንት በመንግሥታቱ የድርጅት ፀጥታ ምክር ቤት የቀረበው የታላቁ የህዳሴ ግድብ ጉዳይ የሶስትዮሽ ድርድሩ ወደ አፍሪካ ህብረት እንዲመለስ የሚል ሀሳብ መቅረቡ ትልቅ ዲፕሎማሲ ስኬት ነው ብለዋል። ቋሚ አባላትም ሁሉም በሚባል […]

ልጆቿን የምታስርብ ሃገር ልትለማ አትችልም-ወይዘሮ ፍሬዓለም ሽባባው

አዲስ አበባ ፣ ሃምሌ 2፣ 2013 በህፃናት ምገባ ላይ ትኩረቱን ያደረገው ስኩል ሚል ኢኒሸቲቭ የተማሪዎችን የምግብ እጥረት ለመቅረፍ የድርሻችንን እንወጣ ሲል ጥሪ አቀረበ፡፡ ድርጅቱ ይህን ያለው በተማሪዎች የምገባ ፕሮግራም የተሰሩትን ሥራዎች ማሳያና የምስጋና መርሐ ግብር ባካሄደበት ወቅት ነው። የስኩል ሚል ኢኒሸቲቭ ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ፍሬዓለም ሽባባው ሃገር የምትለማው ዜጎቿን ስትንከባከብ ነው ብለዋል። ልጆች ባሉበት ሁሉ […]

ኢትዮጵያ በግድቡ ዙሪያ ግልፅ መርህ አስቀምጣ እየተጓዘች ነው-ኢንጅኔር ስለሺ በቀለ

አዲስ አበባ ፣ ሃምሌ 6፣ 2013 ኢትዮጵያ በግድቡ ዙሪያ ግልፅ መርህ አስቀምጣ እየተጓዘች ነው-ኢንጅኔር ስለሺ በቀለ የውኃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጅነር ስለሺ በቀለ ለተባበሩት መንግሥታት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በታላቁ የህዳሴ ግድብ ዙሪያ ማብራርያ ሰጡ፡፡ ሚኒስትሩ ለዋና ጸሐፊው ግንባታው ስላለበት ሁኔታ፣ ስለሁለተኛ ዙር የውኃ ሙሌት እንዲሁም በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት ስለሚካሄደው ድርድር ተገቢውን ማብራሪያ ሰጥተዋል ። […]

የአማራ ጠቅላይ ፍርድ ቤት በባለ ስልጣናት ግድያ በተጠረጠሩ ግለሰቦች ላይ የመከላከያ ምስክሮችን መስማት ጀመረ፡፡

አዲስ አበባ ፣ ሃምሌ 6፣ 2013   የአማራ ጠቅላይ ፍርድ ቤት በባለ ስልጣናት ግድያ በተጠረጠሩ ግለሰቦች ላይ የመከላከያ ምስክሮችን መስማት ጀመረ፡፡ ፍርድ ቤቱ በሰኔ 15 ቀን 2011 ዓ.ም. በአማራ ክልል ባለስልጣናት ግድያ እጃቸው አለበት በተባሉት በእነሻምበል መማር ጌትነት መዝገብ የተከሰሱ 32 ተከሳሾችን የመከላከያ ምስክሮች ነው ማዳመጥ የጀመረው፡፡ በዚሁ የክስ መዝገብ ጉዳያቸው ሲታይ ከነበሩት 55 ተከሳሾች […]

ግብፅ የሙስሊም ወንድማማቾች ህብረት አባላት ላይ የዕድሜ ልክ እስራ  ውሳኔ አስተላለፈች፡፡

አዲስ አበባ ፣ ሃምሌ 6፣ 2013 ግብፅ የሙስሊም ወንድማማቾች ህብረት አባላት ላይ የዕድሜ ልክ እስራ  ውሳኔ አስተላለፈች፡፡ የሀገሪቱ ከፍተኛ ይግባኝ ሰሚ ችሎት የፖሊስ አባላትን በመግደልና እስር ቤት ሰብረው እስረኞችን በማስመለጥ ወንጀል በተከሰሱ የህብረቱን መሪ ሞሐመድ ባዴን ጨምሮ በ10 ግለሰቦች ላይ ነው ወሳኔውን ያሳለፈው፡፡ ተከሳሾቹ እንደ አውሮፓያኑ አቆጣጠር በ2011 በግብፅ በተቀሰቀሰው አብዮት 20 ሺህ የሚሆኑ እስርኞችን እንዲያመልጡ […]

ሁለተኛው ዙር የኮሮናቫይረስ ክትባት ከነገ ጀምሮ በጤና ተቋማት ይሰጣል-ጤና ሚኒስቴር

አዲስ አበባ ፣ ሃምሌ 6፣ 2013 ሁለተኛው ዙር የኮሮናቫይረስ ክትባት ከነገ ጀምሮ በጤና ተቋማት ይሰጣል-ጤና ሚኒስቴር በአዲስ አበባ በአስራ አንዱም ክፍለ ከተሞች ባሉ የጤና ተቋማት ለኮሮና ቫይስ ተጋለጭ የሆኑ የህበረተሰብ ክፍሎች እንዲከተቡ ጤና ሚኒስቴር ጥሪ አቀረበ በአዲስ አበባ የመጀመሪያውን የኮቪድ ክትባት ከወሰዱ ሶስት ወር የሞላቸው ዜጎች ከነገ ጀምሮ እንደሚከተቡ እና በክልሎች ደግሞ ክትባቱን ከሐምሌ 9 […]

በኢራቅ በኮሮና ቫይረስ ማገገሚያ ማዕከል በተነሳ የእሳት አደጋ የበርካታ ሰዎች ህይዎት ማለፉ ተሰማ፡፡

አዲስ አበባ ፣ ሃምሌ 6፣ 2013 በኢራቅ በኮሮና ቫይረስ ማገገሚያ ማዕከል በተነሳ የእሳት አደጋ የበርካታ ሰዎች ህይዎት ማለፉ ተሰማ፡፡ በማገገሚያ ማዕከሉ በተቀሰቀሰው ቃጠሎ ከ64 በላይ ሰዎች ለህልፈት ሲዳረጉ 70 የሚሆኑት ደግሞ ቀላልና ከባድ ጉዳት እንደደረሰባቸው የሀገሪቱ ፖሊስ ይፋ አድርጓል፡፡ ፖሊስ የእሳት አደጋው መንስኤ በውል ባይታወቅም በሆስፒታሉ የሚገኝ ኦክስጂን መፈንዳት የአደጋው ሳይሆን እንዳልቀረ ነው የገለጸው፡፡ አደጋውም […]

የአማራ ክልል በህወሓት ላይ የተጀመረው “ሕግን የማስከበር” ትግል ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቀረበ::

አዲስ አበባ ፣ ሃምሌ 7፣ 2013  የአማራ ክልል በህወሓት ላይ የተጀመረው “ሕግን የማስከበር” ትግል ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቀረበ:: በትግራይ ክልል በህወሓት ላይ የተጀመረው ሕግን የማስከበር ትግል ተጠናክሮ እንዲቀጥል የኢትዮጵያ ሕዝብ አስፈላጊውን ርብርብ እንዲያደርግ የአማራ ክልል ጠየቀ፡፡ ክልሉ ትናንት ባወጣው መግለጫ “ትህነግ አገር ከማፍረስ እኩይ ተልዕኮው ሊታቀብ የሚችለው የአገራችንን ሉአላዊነትና የግዛት አንድነት በጽናትና በአላማ ቁርጠኝነት በጋራ […]

የሲሚንቶ ግብይትን ለመቆጣጣር የወጣው መመሪያ ከዛሬ ጀምሮ ተነሳ::

አዲስ አበባ ፣ ሃምሌ 7፣ 2013  የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የሲሚንቶ ግብይትን ለመቆጣጣር የወጣው መመሪያ ከዛሬ ጀምሮ መነሳቱን አስታወቀ፡፡ በዚህ መሰረት የግብይት ሂደቱ በነፃ ገበያ መርህ እንዲከናወን ተወስኗል ብሏል። የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የንግድ እቃዎች ዋጋ ጥናት ክትትልና ቁጥጥር ዳይሬክተር አቶ ካሳሁን ሙላት፥ በሲሚንቶ ግብይት ላይ ይነሱ የነበሩ ቅሬታዎችን ለመፍታት ሲባል ወደ ቀደመ የነፃ ገበያ አሰራር ተመልሰናል […]

የቀጥታ በረራም ሆነ ከአውሮፕላን ላይ እርዳታ መጣል የሚለው ሀሳብ ተቀባይነት የላቸዉም::

አዲስ አበባ ፣ ሃምሌ 8፣ 2013 ለትግራይ ክልል የሰብዓዊ ድጋፍ በቀጥታ በረራም ሆነ የሀገር ሉዓላዊነትን በሚጥስ ሌላ ተግባር የሚደረግ እንቅስቃሴ አይፈቀድም ተባለ:: የብሔራዊ የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽነር ምትኩ ካሳ በተለይ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት፤ በዓለም ምግብ ፕሮግራምና ሌሎች ዓለም አቀፍ የእርዳታ ተቋማት በኩል ምግብና ምግብ ነክ ያልሆነ የእርዳታ አቅርቦቶች በተገቢው መንገድ ወደ መቀሌ እንዲያጓጓዙ […]