loading
በጥቂት ዓመታት በመላው ኢትዮጵያ 20 ቢሊዮን ችግኞች  እንደሚተከሉ  ጠቅላይ ሚኒሰትር ዐቢይ ተናገሩ፡፡

በጥቂት ዓመታት በመላው ኢትዮጵያ 20 ቢሊዮን ችግኞች  እንደሚተከሉ  ጠቅላይ ሚኒሰትር ዐቢይ ተናገሩ፡፡ አዲስ አበባ፣ ግንቦት 5፣ 2012 ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት፣ የዚህን ዓመት የ አረንጓዴ አሻራ   የችግኝ ተከላ ቅድመ ዝግጅት በተመለከተ የግብርና ሚኒስቴር ማብራሪያ አቅርቧል፡፡የብሔራዊ አስተባባሪ ኮሚቴው አባላት፣ የቴክኒክ ኮሚቴ አባላት፣ የክልል ፕሬዚደንቶች፣ ሕዝቡን የማነሳሳት ሥራን የሚከውኑ ተጽዕኖ አሳዳሪ ግለሰቦችን ጨምሮ ዐበይት ባለድርሻ አካላት ተሳትፈውበታል፡፡ባለፈው […]

በኢትዮጵያ ወጣቶች ለኮሮና ቫይረስ ይበልጥ ተጋላጭ መሆናቸዉን የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዮትአስታወቀ፡፡

በኢትዮጵያ ወጣቶች ለኮሮና ቫይረስ ይበልጥ ተጋላጭ መሆናቸዉን የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዮትአስታወቀ፡፡ አዲስ አበባ፣ ግንቦት 5፣ 2012  ኢንስቲትዩቱ እንዳስታወቀዉ በኢትዮጵያ አስከ ማክሰኞ ዕለት በኮሮና ቫይረስ ከተያዙ 261   ሰዎች መካከል 91 የሚሆኑት እድሜያቸዉ ከ15- 24 ዓመት መሆኑን የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዮት ያወጣዉ አህዛዊ መረጃ ይጠቁማል፡፡ከ25 -34 ባሉት የእድሜ ክልል ዉስጥ ያሉት ደግሞ በሁለተኛ ደረጃ ተጋላጭ  መሆናቸዉን ነዉ መረጃዉ ያመላከተዉ […]

ጀርመን የኮሮና ወረርሽኝን ለመከላከል የቁሳቁስ ድጋፍ አደረገች::

ጀርመን የኮሮና ወረርሽኝን ለመከላከል የቁሳቁስ ድጋፍ አደረገች:: አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 5 ፣ 2012 የጀርመን መንግሥት በኢትዮጵያ የኮሮና ወረርሽኝን ለመከላከል የቁሳቁስ ድጋፉን ለሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር አስረክቧል።ድጋፉ በኢትዮጵያ የኮሮና ወረርሽን ለመከላከል ተግባራዊ ካደረጋቸው የድጋፍ ማዕቀፎች መካከል አንዱ  መሆኑ ተገልጿል።በኢትዮጵያ የጀርመን አምባሳደር ብሪታ ዋግነር ለሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትሯ ፕሮፌሰር ሒሩት ወልደማሪያም ነዉ ድጋፉን ያስረከቡት ፡፡ቫይረሱ በዓለም ላይ ጉዳት እያደረሰ መሆኑን  ያስታወሱት አምባሳደሯ፤አገራቸው ኢትዮጵያን ለመርዳት ድጋፉን ማድረጓን ገልጸዋል። የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትሯ ፕሮፌሰር ሒሩት ወልደማሪያም በዚሁ ወቅት እንደገለጹት ጀርመን የኮሮና ወረርሽኝን ለመዋጋት ላደረገችው ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።ፕሮፌሰርሂሩት፤ሳሙና የእጅ መታጠቢያ 213 ሺህ ኢንፍራሬድ ቴርሞሜትር 50 ያሕል ሰራተኞችችን ከቤታቸው ሆነው እንዲሰሩ የሚያስች ዋይፋ አፓራተስ አበርክተውልናል። እነዚህ ቁሳቁስ ለቴክኒክና ሙያ ተቋሞችና ለዩኒቨርሲቲዎች የምናሰራጫቸው ይሆናል።ብለዋልድጋፉ በትምህርት ተቋማት ወረርሽኙን ለመከላከል የሚደረገውን ጥረት እንደሚያግዝ ተገልጿል፡፡

ህገ ወጥ የጦር መሳሪያ ዝውውርን በመቆጣጠር በኩል ውጤታማ ስራ ተከናውኗል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ገለፁ::

አዲስ አበባ፣ግንቦት6፣2012 ህገ ወጥ የጦር መሳሪያ ዝውውርን በመቆጣጠር በኩል ውጤታማ ስራ ተከናውኗል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ገለፁ:: ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ባለፉት ጥቂት ወራት ህገ ወጥ የጦር መሳሪያ ዝውውርን በመቆጣጠር በኩል ውጤታማ ስራ መከናወኑን ገለጹ።ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፌስቡክ ገፃቸው ባስተላለፉት መልእክት ባለፉት ጥቂት ወራት ሕገ ወጥ የጦር መሣሪያ አዘዋዋሪዎችን ተከታትሎ በመያዝ አኩሪ ሥራ ተሠርቷል። […]

በኢትዮጵያ በ24 ሰዓታት ውስጥ በተደረገ የላቦራቶሪ መምርመራ 14 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኘባቸው

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 11፣ 2012 በኢትዮጵያ በ24 ሰዓታት ውስጥ በተደረገ የላቦራቶሪ መምርመራ 14 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኘባቸው የጤና ሚኒስቴር በመግለጫው እንዳስታወቀው በ24 ሰዓታት ውስጥ በ3 ሺህ 271 ሰዎች ላይ በተደረገ ምርመራ ነው ታማሚዎቹ የተለዩት፡፡ በቫይረሱ የተያዙት ሁሉም ኢትዮጵያዊያን ሲሆኑ እድሜያቸው ከ9 እስከ 65 ዓመት የዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ 11 ወንዶችና 3 ሴቶች መሆናቸው ታውቋል፡፡ በምርመራ […]

ኮቪድ 19ን ተከላክለን የተሻለች ሀገር ለመገንባት ባለን ሀብት ላይ እውቀትና ፈጠራን አቀናጅተን መጠቀም ይኖርብናል አሉ ጠ/ሚ ዐቢይ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 11፣ 2012 ኮቪድ 19ን ተከላክለን የተሻለች ሀገር ለመገንባት ባለን ሀብት ላይ እውቀትና ፈጠራን አቀናጅተን መጠቀም ይኖርብናል አሉ ጠ/ሚ ዐቢይ:: ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በፌስቡክ ገፃቸው ፈጠራን በተመለከተ ባስተላለፉት መልእክት፥ ብዙዎቹ የፈጠራ ውጤቶች የፈተና ልጆች ናቸው ይባላል ብለዋል። የሰው ልጆች ከዛሬው ሥልጣኔያቸው ላይ የደረሱት በየዘመናቱ የተደቀኑባቸውን እንቅፋቶች ለማለፍ እውቀትና ክሎታቸውን በስፋት በመጠቀማቸው […]

ለኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ ቀጥሏል::

ለኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ ቀጥሏል ። የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ወደ ወሳኝ ምዕራፍ በተሸጋገረበት ወቅት የህዝቡ ሁለንተናዊ ተሳትፎ እያደገ መምጣቱን የአማራ ክልል የታላቁ ህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ምክር ቤት ጽህፈት ቤት አስታወቀ። የጽህፈት ቤቱ ሃላፊ አቶ ላቀ ጥላዬ ለኢዜአ እንደገለጹት የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ማጠናቀቅ የአገራችን ሉአላዊነትና የፍትሃዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ ጉዳይ ነው። መንግስትና ህዝብ […]

1441ኛው የኢድ አል-ፊጥር በዓል አርብ ምሽት ጨረቃ ከታየች ቅዳሜ ካልሆነ ግን እሁድ ይከበራል፡፡

1441ኛው የኢድ አል-ፊጥር በዓል አርብ ምሽት ጨረቃ ከታየች ቅዳሜ  ካልሆነ ግን እሁድ እንደሚከበር የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት አስታዉቋል፡፡የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጅ ኡመር ኢድሪስ ለምእመናን የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡ በዕለቱ የጀምዓ ሶላት እንደማይኖር የገለጹት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጅ ኡመር ምእመናን በዓሉን በየቤታቸው እንዲያከብሩት አሳስበዋል፡፡  ምእመናን በዓሉን የተራቡትን በማጉረስ፣ የተጠሙትን በማጠጣት በአጠቃላይ የተቸገሩትን በመርዳት እንዲያከብሩም ጥሪ አቅርበዋል፡፡

የጤና ሚኒስቴር የቴንሴንት ፋውንዴሽን የላካቸውን የኮሮና ቫይረስ መመርመሪያ ቁሳቁሶች ተረከበ::

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 14፣2012  ጤና ሚኒስትሯ ዶ/ር ሊያ ታደሰ እነዳስታወቁት  የቴንሴንት በጎ አድራጎት ድርጅት ኮቪድ19 ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚሰራውን ስራ ለማገዝ የሚያስችሉ 1ነጥብ6 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጡ የመመርመሪያ ኪቶችንና ጓንቶችን ድጋፍአድርጓል፡፡ ዶ/ር ሊያ በጎ አድራጎት ድርጅቱ  ስላደረገልን ድጋፍ ልባዊ ምስጋናዬን እየገለጽኩ ሁሌም ትብብራቸው የማይለየንን በኢትዮጵያ የቻይና ኤምባሲ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድን ላመሰግንን እወዳለሁ ብለዋል  በፌስቡክ ገጻቸዉ፡፡ የቴንሴንት ኩባንያ የታዋቂው […]

የኮሮና በሽታን ለመከላከል የሚያስችሉ ፈጠራዎችን ያቀረቡ ተወዳዳሪዎች እውቅና እና ሽልማት ተበረከተላቸዉ፡፡

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 14፣2012  የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከተባበሩት መንግስታት የልማት ፕሮግራም ጋር ባደረጉት የድጋፍ ስምምነት እና በመንግስት እገዛ ሲካሄድ የነበረው የኮቪድ 19 ቴክኖሎጂ ሶሊዩሽን ቻሌንጅ ዉድድር ተለይተዉ ታዉቀዋል።  በአጭር  ጊዜ ተተግባሪና መፍትሔ ሊያመጡ የሚችሉት ምርጥ ፕሮጀክቶች ተለይተው እውቅና ተሰጥቷቸዋል። ፍጻሜውን ያገኘውን የውድድር ሂደት በንግግር የከፈቱት የኢኖቬሽን ምርምር ዘርፍ ሚኒስቴር ዲኤታ አቶ ሲሳይ ቶላ በችግር […]