loading
ኮቪድ 19ን ተከላክለን የተሻለች ሀገር ለመገንባት ባለን ሀብት ላይ እውቀትና ፈጠራን አቀናጅተን መጠቀም ይኖርብናል አሉ ጠ/ሚ ዐቢይ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 11፣ 2012 ኮቪድ 19ን ተከላክለን የተሻለች ሀገር ለመገንባት ባለን ሀብት ላይ እውቀትና ፈጠራን አቀናጅተን መጠቀም ይኖርብናል አሉ ጠ/ሚ ዐቢይ:: ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በፌስቡክ ገፃቸው ፈጠራን በተመለከተ ባስተላለፉት መልእክት፥ ብዙዎቹ የፈጠራ ውጤቶች የፈተና ልጆች ናቸው ይባላል ብለዋል። የሰው ልጆች ከዛሬው ሥልጣኔያቸው ላይ የደረሱት በየዘመናቱ የተደቀኑባቸውን እንቅፋቶች ለማለፍ እውቀትና ክሎታቸውን በስፋት በመጠቀማቸው […]

ለኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ ቀጥሏል::

ለኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ ቀጥሏል ። የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ወደ ወሳኝ ምዕራፍ በተሸጋገረበት ወቅት የህዝቡ ሁለንተናዊ ተሳትፎ እያደገ መምጣቱን የአማራ ክልል የታላቁ ህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ምክር ቤት ጽህፈት ቤት አስታወቀ። የጽህፈት ቤቱ ሃላፊ አቶ ላቀ ጥላዬ ለኢዜአ እንደገለጹት የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ማጠናቀቅ የአገራችን ሉአላዊነትና የፍትሃዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ ጉዳይ ነው። መንግስትና ህዝብ […]

ጄምኮርፕ ኩባንያ የብሔራዊ የአደጋ መከላከያ እና ዝግጁነት ኮሚሽን አደጋን ለመቀነስ ለሚያደርገዉ ዝግጅት ድጋፍ እያደረኩኝ ነዉ አለ፡፡

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 17፣ 2012 ጄምኮርፕ ኩባንያ የብሔራዊ የአደጋ መከላከያ እና ዝግጁነት ኮሚሽን አደጋን ለመቀነስ ለሚያደርገዉ ዝግጅት ድጋፍ እያደረኩኝ ነዉ አለ፡፡ ኩባንያዉ የብሔራዊ የአደጋ መከላከያ እና ዝግጁነት ኮሚሽን 200,000 ሜትሪክ ቶን ስንዴ ለመግዛት ላወጣው ጨረታ ተወዳዳሪ ሆኖ በመገኘት በድጋሚ ማሸነፉን ለአርትስ በላከዉ መግለጫ አስታዉቋልጄምኮርፕ ኢኮኖሚውን በንግድ ሥራ ለመደገፍ እና ኢንቨስት ለማድረግ የኢትዮጵያን ገበያ የተቀላቀለው በ2010ዓ.ም. […]

አስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ምክንያት በማድረግ በትግራይ ክልል እየተፈፀመ ያለዉ ግፍ እንዲቆም ህጋዊ መፍትሄ እንደሚያስፈልገዉ የትግራይ ብልፅግና ፓርቲ ለአርትስ ቲቪ ገለፀ ፡፡

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 17፣ 2012 አስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ምክንያት በማድረግ በትግራይ ክልል እየተፈፀመ ያለዉ ግፍ እንዲቆም ህጋዊ መፍትሄ እንደሚያስፈልገዉ የትግራይ ብልፅግና ፓርቲ ለአርትስ ቲቪ ገለፀ ፡፡በክልሉ አሁን ድረስ ቀደም ሲል የነበረዉ የአፈናና የእኔ አዉቅልሀለሁ አገዛዝ አሁንም እንደቀጠለ የተናገሩት የፓርቲዉ ከፍተኛ አመራሮችና አባላት በተለይ የትግራይ ህዝብን ከመላዉ የኢትዮጵያ ህዝብ ለመነጠል የሚደረገዉ ጥረት ተቀባይነት እንደሌለዉ ተናግረዋል፡፡በመሆኑም በክልሉ […]

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 19 ፣ 2012ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የኳታር መንግስት ለኢትዮጵያ የሕክምና ቁሳቁሶችን ድጋፍ በማድረጉ አመሰገኑ::

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 19 ፣ 2012ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የኳታር መንግስት ለኢትዮጵያ የሕክምና ቁሳቁሶችን ድጋፍ በማድረጉ አመሰገኑ:: “የኳታር መንግሥት የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭንብሎች፣ የሕክምና ጓንቶች፣ ፊትን ሙሉ በሙሉ የሚሸፍኑ እና ሰውነትን ከንክኪ የሚከላከሉ ልብሶች እንዲሁም ሌሎች ኮቪድ-19ን የመከላከያ ግብአቶች መላካችሁ  ወረርሽኙን ለመግታት የምናደርገውን ጥረት ይደግፋል ነዉ ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፡፡ድጋፉ 470 ሺ ማስክ ፣ 70 […]

ለኮሮና ቫይረስ መከላከል ድጋፍ የሚውል ከ500 ሺህ በላይ ማስክና የገንዘብ ድጋፍ ተበረከተ።

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 25፣ 2012 ለኮሮና ቫይረስ መከላከል ድጋፍ የሚውል ከ500 ሺህ በላይ ማስክና የገንዘብ ድጋፍ ተበረከተ። በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ከ6 የቻይና ተቋማት የተሰባሰቡ 500 ሺህ ማስኮችና የተለያዩ ቁሳቁሶችን ለከተማ አስተዳደሩ አበርክተዋል። የተለያዩ ኢትዮጵያውያን ተቋማትም 1ነጥብ 1 ሚሊየን ብር ድጋፍ ያደረጉ ሲሆን በተጨማሪም 180 ሺህ ብር የሚገመት በእግር የሚሰራ እጅ መታጠቢያ ድጋፍ ተደርጓል። ድጋፉን የተረከቡት […]

በኢትዮጵያ የኮሮናቫይረስ መመርመሪያ ማዕከላት ቁጥር 46 ደረሰ፡፡

በኢትዮጵያ የኮሮናቫይረስ መመርመሪያ ማዕከላት ቁጥር 46 ደረሰ፡፡የጤና ሚኒስቴር በፌስቡክ ገጹ እንዳስታወቀዉ የኮሮና ቫይረስ ኢትዮጵያ መግባቱ ሲረጋገጥ ምንም ዓይነት የመመርመሪያ ማዕከል ያልነበራት ኢትዮጵያ በአሁን ወቅት 46 ማዕከላት አላት ብሏል፡፡የጤና ሚኒስቴር ይህን ችግር በመረዳት በአጭር ጊዜ በአገር ውስጥ የመመርመሪያ መሳሪዎችን በሟሟላት እና ባለሙያዎችን በማሰልጠን የላብራቶሪ ምርመራ ማዕከላትን አደራጅቷል፡፡ የሚኒስቴሩ የመመርመር አቅም ከጊዜ ወደጊዜ እየጨመረ እንደመጣም ገልጿል፡፡እስከ ግንቦት […]

ሰብዓዊ መብት የምናከብረውና የምናስከብረው ለማንም ብለን ሳይሆን ለህዝባችንና ለፍትህ ስንል አሉ የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ::

ሰብዓዊ መብት የምናከብረውና የምናስከብረው ለማንም ብለን ሳይሆን ለህዝባችንና ለፍትህ ስንል አሉ የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ:: “ሰብዓዊ መብት የምናከብረውና የምናስከብረው ለማንም ብለን ሳይሆን ለህዝባችንና ለፍትህ ስንል ነው” ሲሉ የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ ገለፁ።ወይዘሮ አዳነች አቤቤ ሰሞኑን አመነስቲ ኢንተርናሽናል በኢትዮጵያ ላይ ይዞ በወጣው ሪፖርት ዙሪያ በፌስቡክ ገፃቸው ባስተላለፉት መልእክት፥ “በአምነስቲ ኢንተርናሽናል […]

ሱዳን ለፀጥታው ምክር ቤት የህዳሴው ግድብ የሶስትዮሽ ድርድር እንዲጀምር የሚያሳስብ ደብዳቤ ላከች::

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 26፣ 2012 ሱዳን ለፀጥታው ምክር ቤት የህዳሴው ግድብ የሶስትዮሽ ድርድር እንዲጀምር የሚያሳስብ ደብዳቤ ላከች:: የሱዳን የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ተደራዳሪዎቹ ኢትዮጵያ፣ ሱዳንና ግብፅ የሶስትዮሽ ውይይቱን በፍጥነት እንዲጀምሩና በተናጠል የሚደረጉ እንቅስቃሴዎች እንዲቆሙ የሚጠይቅ ደብዳቤ ነው የላከው ተብሏል፡፡የውጭ ጉዳይ ሚንስትሯ አሳም ሞሀመድ አብደላ ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት በላኩት ደብዳቤ በድርድሩ ሂደት […]

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በቤይሩት የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ድጋፍ እንዲያገኙ እየሰራሁ ነው አለ::

አዲስ አበባ፣ነሐሴ1፣ 2012 የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በቤይሩት የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ድጋፍ እንዲያገኙ እየሰራሁ ነው አለ:: በሊባኖስ በደረሰዉ ፍንዳታ የ1 ኢትዮጵያዊ ህይወት ማለፉንና 9 ኢትዮጵያዊያን ደግሞ ቀላልና ከባድ አደጋ እንደደረሰባቸዉ የሚኒስሩ ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲን ሙፍቲ ገልፀዋል፡፡ በቤይሩት በሚገኙት መጠለያዎች ዉስጥ ያሉ ኢትዮጵያዊያን ግን ጉዳት እንዳልደረሰባቸዉና በጥሩ ደህንነት እንደሚገኙ ነዉ የተነገረ ሲሆን ወደ ፌት ግን ቁጥሩ ሊጨምር […]