loading
በሳዑዲ አረቢያ ያለመኖሪያ ፈቃድ ይኖሩ የነበሩ ኢትዮጵያዊያን ወደሃገራቸው ተመለሱ 

በሳዑዲ አረቢያ ያለመኖሪያ ፈቃድ ይኖሩ የነበሩ ኢትዮጵያዊያን ወደሃገራቸው ተመለሱ ። እነዚሁ 850 ኢትዮጵያውያን በሁለት ዙር ባሳለፍነው ሳምንት ወደ አገራቸው ተመልሰዋል። ከተመለሻቹ መካከል 445 ያህል ሰዎች ባሳለፍነው አርብ፣ ቀሪዎቹ 405 ደግሞ እሁድ እለት ወደሀገራቸው የገቡ ናቸው። ከስደት ተመላሾቹ ወደ ሀገራቸው የተመለሱት በራሳቸው ፈቃድ ሲሆን ሳዑዲ አረቢያ የገቡትም ቀይ ባህርን አቋርጠው በህገ-ወጥ መንገድ እንደነበር ተነግሯል። ተመላሾቹ ወደ ሀገራቸው […]

በሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር እና በሃይማኖት ተቋማት መካከል ስመምነት ተፈረመ

የሀይማኖት ተቋማት ለዜጎች በተናጥል የሚያደርጉትን ድጋፍ ውጤት በሚያመጣ መልኩ ለማቀናጀት የሚያስችል ነው የተባለ የመግባቢያ ስምምነት በሃይማኖት ተቋማትና በሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ተፈረመ። ሚኒስቴር መስሪያቤቱና  የሃይማኖት ተቋማት አረጋውያንን፣ አካል ጉዳተኞችን እና ለማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ተጋላጭ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚነትና ተሳታፊነት ለማረጋገጥ የሚያስችል የመግባቢያ ሰነድ ጋር መፈራረማቸውን የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። ስምምነቱ ለማህበራዊ እና […]

“ሃገሪቷ ያሏት ቅርሶች ብዛት ከእንክብካቤ እና እድሳት አቅም በላይ ነው” – ዶክተር ሂሩት ካሳው

በኢትዮጵያ ቅርሶችን ለመጠገን እና ለማደስ አስቸጋሪ የሆነው  ሃገሪቱ ያሏት ቅርሶች ብዛት ካላት የመንከባከብ  አቅም ጋር ስላልተመጣጠነ መሆኑን የባህል እና ቱሪዝም ሚኒስትር ዶ/ር ሂሩት ካሳው ተናገሩ። ሚኒስትሯ ይህን ያሉት በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የሚጠበቅበትን ሃላፊነት ለመወጣት ያደረገውን ጥረት እና የገጠሙትን ችግሮች በሚመለከት ለጋዜጠኞች መግለጫ በሰጡበት ወቅት ነው፡፡ ዶ/ር ሂሩት በመግለጫቸው በሀገራችን የቅርሶች ቁጥር […]

የሴቶችን ተጠቃሚነት እና እኩልነትን ለማረጋገጥ የተቀናጀና ትብብርን መሰረት ያደረገ እንቅስቃሴ” ፕሬዚዳንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ

በኢትዮጵያ የሴቶችን ተጠቃሚነት እና እኩልነትን ለማረጋገጥ የሚከናወኑ ተግባራትን ውጤታማ ለማድረግ የተቀናጀና ትብብርን መሰረት ያደረገ እንቅስቃሴ እንደሚያስፈልግ ፕሬዚዳንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ አስገነዘቡ። “መተባበር ለላቀ ውጤት” በሚል ርዕስ የተዘጋጀው እና በሥርዐተ ጾታ እኩልነት እና ሴቶችን በማብቃት ዙሪያ የሚሰሩ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የውይይት መድረክ በአፍሪካ ኢኮኖሚክ አዳራሽ ዛሬ ረፋድ ላይ ሲጀመር ፕሬዚዳንቷ እንዳሉት በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ የተፈጠረውን መልካም […]

ለ5 ዓመታት ተቋርጦ የነበረው የመካከለኛው ምስራቅ ሃገራት የአሰሪ እና ሰራተኛ ጉዞ የአሻራ ምርመራ አገልግሎት ተጀመረ

ለ5 ዓመታት ተቋርጦ የነበረው የመካከለኛው ምስራቅ ሃገራት የአሰሪ እና ሰራተኛ ጉዞ የአሻራ ምርመራ አገልግሎት ተጀመረ። ለ5 ዓመታት ተቋርጦ የነበረውን የመካከለኛው ምስራቅ ሃገራት የአሰሪ እና ሰራተኛ ጉዞ የፎረንሲክ ምርመራ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡ ኮሚሽኑ አገልግሎቱን  ሚያዚያ 14/2011 ጀምሮ መስጠት መጀመሩን አስታውቋል፡፡ አገልግሎቱ ወደ መካከለኛው ምስራቅ አገራት ተቋርጦ የነበረው የአሰሪ እና ሰራተኛ ጉዞ በሰራተኛና […]

በሶስት የጉምሩክ መቆጣጠሪያ ጣቢያዎች 990 ሺህ ብር የሚጠጋ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ ዕቃዎች ተያዙ

በሶስት የጉምሩክ መቆጣጠሪያ ጣቢያዎች 990 ሺህ ብር የሚጠጋ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ ዕቃዎች ተያዙ የገቢዎች ሚኒስቴር እንዳስታወቀው ግምታቸው 989,800 ብር የሆኑ ልዩ ልዩ የኮንትሮባንድ ዕቃዎች በቁጥጥር ስር የዋሉት በአርበረከቴ ፣ በቶጎጫሌ እና  በሐረር የመቆጣጠሪያ ጣቢያዎች  ነው።   አርበረከቴ መቆጣጠሪያ ጣቢያ በአህዮች ተጭኖ ሲጓጓዙ በቁጥጥር ስር የዋሉት ኮንትሮባንድ እቃዎች መድሃኒት፣ መነፅርና አልባሳት ሲሆኑ በቶጎጫሌ መቆጣጠሪያ ጣቢያ ደግሞ […]

የ2011 የአለም የወባ ቀንን በማስመልከት የተዘጋጀው ፕሮግራም በድሬደዋ ተጀመረ

የ2011 የአለም የወባ ቀንን በማስመልከት የተዘጋጀው ፕሮግራም በድሬደዋ ተጀመረ። በጤና ሚኒስቴር የበሽታዎች መከላከልና መቆጣጠር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ህይወት ሰለሞን እንደገለፁት በአለም አቀፍ ደረጃ የተጀመረውን የወባ ማጥፋት ዘመቻ የተቀላቀለችው ኢትዮጵያ በስድስት ክልሎችና 239 ወረዳዎች የዘረጋችው መርሀ ግብር ውጤታማ መሆኑ ተነግሯል የድሬደዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ሀላፊ ዶ/ር ፉአድ ከድር በበኩላቸው ከአሁን ቀደም በድሬደዋ ነዋሪዎች በእለት ተእለት ኑሮ […]

‹‹የሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ ቃጠሎ ሆን ተብሎ የተቀነባበረ ነው›› አቶ ግርማ ቲመር የዱር እንሰሳ ጥበቃ ቦታዎች ልማት ዳይሬክተር

በሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ ተከስቶ የደን የእሳት ቃጠሎ መነሻ ሆን ተብሎ በሰዎች አማካኝነት የተለቀቀ እሳት መሆኑን የዱር እንሰሳት ልማት እና ጥበቃ ባለስልጣን ለአርትስ ቲቪ አረጋገጠ። ‹‹የሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ ቃጠሎ ሆን ተብሎ የተቀነባበረ ነው›› ብለዋል አቶ ግርማ ቲመር የዱር እንሰሳ ጥበቃ ቦታዎች ልማት ዳይሬክተር ከአርትስ ቲቪ ጋር በነበራቸው ቆይታ። ከፓርኩን ቃጠሎ ጋር በተያያዘ ምርመራ እየተደረገ […]

መንግሥት የሚደጉመው የፓልም ዘይት የጤናችግር  ስለሚያመጣ በሌሎች ፈሳሽ ዘይቶች እንዲቀየር ጤና ሚኒስቴር ጠየቀ

መንግሥት የሚደጉመው የፓልም ዘይት የጤናችግር  ስለሚያመጣ በሌሎች ፈሳሽ ዘይቶች እንዲቀየር ጤና ሚኒስቴር ጠየቀ። ከፍተኛ የጤና ችግር ያመጣል የተባለው የፓልም ዘይት ከ90 እስከ 95 በመቶ በድጎማ የሚገባ ሲሆን፣ ይህንን ለመቀየር መጠየቁን ነው ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ያስታወቀው፡፡ ሚኒስቴሩ የኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩትና የመድኃኒትና ምግብ ቁጥጥር ባለሥልጣን ያቀረባቸውን ጥናቶች ምክረ ሐሳብ መሠረት በማድረግ፣ የፓልም ዘይት በፈሳሽ ዘይቶች እንዲቀየር ለጠቅላይ […]