loading
ስምንት የግብጽ ወታደሮች በፀረ ሽብርተኝነት ተልዕኮ ላይ ሳሉ መገደላቸው ተገለፀ፡፡

አዲስ አበባ ፣ ሃምሌ 26፣ 2013 ስምንት የግብጽ ወታደሮች በፀረ ሽብርተኝነት ተልዕኮ ላይ ሳሉ መገደላቸው ተገለፀ፡፡ ስምንቱ ግብጻውያን ወታደሮች በጸረ ሽብርተኝነት ተልዕኮ በነበሩበት መገደላቸውን የጦሩ ቃል አቀባይ ለሮይተርስ ተናግረዋል፡፡ እንደ ወታደራዊ ሃይሉ መግለጫ በአብዛኛው ውጊያው እየተካሄደ የነበረው የታጠቁ የዳኢሽ ቡድኖች በሚንቀሳቀሱበት ሰሜናዊ ሲናይ በረሃ ላይ እንደነበር ተገልጿል፡፡ ወታደሮቹ በሙሉ እዚያ ይሁን በሌላ ስፍራ ስለመሞታቸው ግን […]

ሳማንታ ፓወር በኢትዮጵያ በነበራቸው ቆይታ ገንቢ ሀሳቦችን አንስተዋል::

አዲስ አበባ ፣ ሃምሌ 29፣ 2013 የዩ ኤስ ኤድ ኃላፊ ሳማንታ ፓወር በኢትዮጵያ በነበራቸው ቆይታ ገንቢ ሀሳቦች ማንሳታቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለፀ:: የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምበሳደር ዲና ሙፍቲ በሰጡት ሳምንታዊ መግለጫ ሳማንታ ፓወር በኢትዮጵያ በነበራቸው ቆይታ ገንቢ ሀሳቦች ማንሳታቸውን ተናግረዋል፡፡ በኢትዮጵያ በተለይም በትግራይ ክልል መንግስት እየሰራቸው ያሉ የሰብዓዊ እርዳታ ስራዎችን ከሰላም ሚኒስትሯ ወ/ሮ […]

ዩ ኤስ ኤድ የኮቪድ 19 ስርጭትን ለመግታት የሚውል 720 ሚሊዮን ዶላር ይፋ አደረገ::

አዲስ አበባ ፣ ሃምሌ 29፣ 2013 ዩ ኤስ ኤድ የኮቪድ 19 ስርጭትን ለመግታት የሚውል 720 ሚሊዮን ዶላር ይፋ አደረገ:: ዩ ኤስ ኤድ የተሰኘው የአሜሪካ ዓለምአቀፍ ተራድኦ ድርጅት ለኮቪድ 19 ምላሽ እና ማገገሚያ የሚውል 720 ሚሊዮን ዶላር ማፅደቁ ተሰማ፡፡ የአሜሪካ ዓለምአቀፍ ተራድኦ ድርጅት ኃላፊ ሳማንታ ፓወር እንደገለፁት በጀቱ የኮቪድ 19 ስርጭትን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለመግታት ያለመ […]

አልማ ማህበር የህወሓት ቡድን በፈጠረ ቀውስ ምክንያት ለተፈናቀሉ ወገኖች የዕለት ደራሽ ድጋፍ አቀረበ::

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 3፣ 2013 የአማራ ልማት ማህበር ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አራጋው ታደሰ እንደገለፁት በዋግ ህምራና ሰሜን ወሎ አስተዳደር ዞን የቆቦ፣ ራያ አላማጣና ግዳን ወረዳ ነዋሪዎች በአሸባሪው ትህነግ ምክንያት ከሰላማዊ ኑሯቸው ተፈናቅለው ደሴና ወልድያ ከተማ ለሚገኙ የዕለት ደራሽ ድጋፍ አቅርበዋል። ተለዋዋጭ ሁኔታዎችን እንደ አስፈላጊነቱ መፈፀም በሚያስችለው ስትራቴጅያዊ የለውጥ ዕቅድ መሰረት ቡድኑ በፈጠረው ቀውስ […]

ሳዑዲ አረቢያ የኮቪድ -19 ክትባት ለወሰዱና ከተለያዩ ሀገራት ለመንፈሳዊ ጉዞ ወደ መካ መዲና የሚገቡ የኡምራ ተጓዦች መቀበል እንደምትጀመር አስታውቃለች ፡፡

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 3፣ 2013 ሳዑዲ አረቢያ የኮቪድ -19 ክትባት ለወሰዱና ከተለያዩ ሀገራት ለመንፈሳዊ ጉዞ ወደ መካ መዲና የሚገቡ የኡምራ ተጓዦች መቀበል እንደምትጀመር አስታውቃለች ፡፡ የሀገሪቱ ባለስልጣናት እንደሚሉት ከሆነ ከሰኞ ጀምሮ የኡምራ ተጓዦችን ጥያቄ መቀበል መጀመራቸውን ነው የገለጹት ፡፡ ሳዑዲ አረቢያ በኮቪድ-19 ስርጭት ምክንያት ለ18 ወራት ከተለያዩ ሀገራት መግቢያ በሮቿን ዝግ አድርጋ ቆይታለች፡፡ አሁን ላይ […]

በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የተማሪዎች ምገባ ሊጀመር ነው::

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 3፣ 2013 በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የተማሪዎች ምገባ መርሃ ግብርን ለመጀመር ጥናት እየተደረገ ነው::በአዲስ አበባ የተማሪዎች ምገባ መርሃ ግብርን በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለማስጀመር ጥናት እየተደረገ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተማሪዎች ምግብ ኤጀንሲ አስታወቀ፡፡ የኤጀንሲው ዳይሬክተር አቶ ኢሳያስ ምህረት ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለፁት÷ በ2014 በጀት ዓመት ለምገባ መርሃ ግብር 1 ነጥብ […]

የውጭ ኃይሎች በኢትዮጵያ ላይ ዘመቻ የከፈቱት መንግሥት ለነሱ ጥቅም ባለመቆሙ ነው- የህግ መምህርና የማህበረሰብ አንቂ ሙክታር ኡስማን::

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 4፣ 2013 አንዳንድ የውጭ ኃይሎች በኢትዮጵያ ላይ ዘመቻ የከፈቱት አሁን ኢትዮጵያን እየመራ ያለው መንግሥት አሸባሪው ህወሓት ስልጣን ላይ እያለ እንደነበረው ለነሱ ጥቅም የቆመ ባለመሆኑ እንደሆነ የህግ መምህርና የማህበረሰብ አንቂው አቶ ሙክታር ኡስማን ተናገሩ። አቶ ሙክታር ለአዲስ ዘመን እንደገለጹት፤ አሁን ስልጣን ላይ ያለው የኢትዮጵያ መንግሥት በራሱ የሚተማመንና እና በምሥራቅ አፍሪካ ለውጥ ለማምጣት መሥራት […]

ለመጀመሪያ ጊዜ በበይነ መረብ ለማስተማር ለ4 ተቋማት ፈቃድ ተሰጠ::

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 4፣ 2013  በበይነ መረብ (ኦንላይን) ትምህርት ለመጀመር ካመለከቱ 9 የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለመጀመሪያ ጊዜ ለ4 ተቋማት የእውቅና ፈቃድ መስጠቱን የከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጀንሲ አስታወቀ። በዚህም አራቱ ተቋማት በመጀመሪያ ዲግሪና በሁለተኛ ዲግሪ በ6 ፕሮግራሞች የእውቅና ፈቃድ እንደተሰጣቸው ነው የኤጀንሲው የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ ታረቀኝ ገረሱ ለኢቲቪ የገለጹት። በበይነ መረብ (ኦንላይን) ለማስተማር ፈቃድ […]

አሸባሪውን የሕወሓትን ኃይል ከታሪክ ገጽ ለመደምሰስ ጊዜው አሁን ነዉ -የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 4፣ 2013 ሀገር በመከላከል ዘመቻው ለመሳተፍ እድሜያችሁና ዐቅማችሁ የሚፈቅድላችሁ ኢትዮጵያውያን ሁሉ የመከላከያ ሠራዊቱን እንዲቀላቀል ጥሪ ቀረበ፡፡ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ባደረገዉ ጥሪ ፣ዐቅማችሁ የሚፈቅድላችሁ ኢትዮጵያውያን ሁሉ የመከላከያ ሠራዊቱን ልዩ ኃይሉንና ሚሊሻውን በመቀላቀል የሀገር ዘብነታችሁን የምታሳዩበት ትክክለኛው ጊዜ አሁን ነው ብሏል፡፡ አሸባሪውን የሕወሓት ኃይል ከታሪክ ገጽ ለመደምሰስ የሀገር መከላከያ ሠራዊታችን፣ የክልል ልዩ ኃይሎችና ሚሊሻዎች፣ […]

ባለፉት ሁለት ቀናት በኢትዮጵያ በኮቪድ- 19 ምክንያት 20 ሰዎች ህይወታቸው አለፈ፡፡

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 6፣ 2013 ባለፉት ሁለት ቀናት በኢትዮጵያ በኮቪድ- 19 ምክንያት 20 ሰዎች ህይወታቸው አለፈ፡፡የጤና ሚኒስቴር የ24 ሰዓታት የኮቪድ-19 መረጃ እንደሚያመለክተው በተከታታይ በሁለት ቀናትውስጥ 20 ሰዎች ህይወታቸውን በቫይረሱ አጥተዋል፡፡ ቫይረሱ ሀገራችን ከገባ ጀምሮም ህይወታቸው በቫይረሱ ያለፈ ሰዎች ቁጥር 4 ሺህ 4 መቶ 50 ደርሷል፡፡የጽኑ ህሙማንም ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ የጨመረ ሲሆን ፤ የ24 ሰዓታቱ ሪፖርት […]