loading
የኢሳት ቴሌቪዥን ጋዜጠኞች ወደ ኢትዮጵያ ገቡ

የኢሳት ቴሌቪዥን ጋዜጠኞች ወደ ኢትዮጵያ ገቡ ለ20 ዓመታት ከሃገር ውጭ የነበሩ የኢሳት ቴሌዥን ጋዜጠኞች በዛሬ ዕለት ወደ ኢትዮጵያ ገብተዋል፡፡ የኢሳት ጋዜጠኞቹን የባህልና ቱሪዝም ሚንስትሯ ዶክተር ሂሩት ካሳሁን እንዲሁም ሌሎች የመንግሥት ባለስልጣናት አቀባበል አድገውላቸዋል። በተጨማሪም የጋዜጠኞቹ ቤተሰቦች፣ አድናቂዎቻቸው እና ደጋፊዎቻቸውም ጭምር በአቀባበል ስነ ስርዓቱ ላይ ተገኝተዋል። ጋዜጠኞቹ በበኩላቸው ወደ ሃገራቸው በመግባታቸው ከፍተኛ ደስታ እንደተሰማቸው እና በሃገሪቱ […]

የኤርትራ ፐብሊክ ዲፕሎማሲና የባህል ልዑክ አዲስ አበባ ገባ

የኤርትራ የባህል እና የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ቡድን አዲስ አበባ ገባ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ አንደሚጠቁመው ከ60 በላይ አባላት ያሉትና ታዋቂው አርቲስት በረኸት መንግስተአብን ጨምሮ የተለያዩ አከላትን ያካተተ የኤርትራ የባህልና የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ቡድን አዲስ አበባ ገብቷል። ቡድኑ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማሪፊያ ሲደርስ ከኢ.ፌ.ዲ.ሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ከባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር እና ከአዲስ አበባ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ […]

የትግራይ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት ለሀገርና ለህዝቦች ሉአላዊነት መከበር ያበረከተውን  አስተዋጽኦ አደነቁ

የትግራይ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት ለሀገርና ለህዝቦች ሉአላዊነት መከበር ያበረከተውን  አስተዋጽኦ አደነቁ።   መከላከያ ሰራዊቱ ለልማትና ለዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ወሳኝ የሆነው የህገ-መንግስትና የህዝቦች ሉአላዊነት ያለምንም መሸራረፍ እንዲከበር በማድረግ አርአያነት ያለው ተግባር እያከናወነ ነው ብለዋል። ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ ዶክተር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል የሃገር መከላከያ ሰራዊት ቀን በዓልን ምክንያት በማድረግ በሰጡት መግለጫ እንዳሉት የሀገራችንና ጎረቤት […]

የመንገድ ፈንድ ጽህፈት ቤት ባለፉት ሰባት ወራት 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር መሰብሰቡን አስታወቀ

የመንገድ ፈንድ ጽህፈት ቤት ባለፉት ሰባት ወራት 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር መሰብሰቡን አስታወቀ፡፡ገቢው ለመንገድ ጥገናና ለመንገድ ደህንነት እርምጃዎች ማስፈጸሚያ ይውላል ብሏል። ጽህፈት ቤቱ ለአርትስ ቲቪ የላከው የተቋሙ የ2011 በጀት አመት የሰባት ወራት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት እንደሚያመለክተው በሰባት ወራት የስራ አፈጻጸሙ  1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ አቅዶ 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር መሰብሰብ ችሏል። […]

ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው  በቤኒሻንጉልና ጋምቤላ ትምህርት ቤቶችን ሊያስገነቡ ነው

ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው  በቤኒሻንጉልና ጋምቤላ ትምህርት ቤቶችን ሊያስገነቡ ነው   ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ በሁለቱ ክልሎች  20 ሚሊዮን ብር ትምህርት ቤቶቹን ለማስገንባት የሚያስችል የመግባቢያ ሰነድ ከሁለቱም ክልሎች ትምህርት ቢሮ ተወካዮች ጋር ተፈራርመዋል።   እንደ ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ገለፃ ለዜጎች ጥራት ያለው ትምህርት ፍትሃዊ በሆነ ሁኔታ ተደራሽማድረግ የሀገሪቱን የወደፊት ትውልድ ለማነጽ እና ለማዘጋጀት ቁልፍ ተግባር ነው ።   በተያያዘ ዜናም ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው የተለያዩ የውጭ ሀገር ተቋማትን በማስተባበር ያሰባሰቧቸውን የህክምና መገልገያ ቁሳቁሶች የህፃናት አልጋዎች፣የደም ማስቀመጫ ፍሪጆች  እና ተሽከርካሪ የሆስፒታል ወንበሮች ለሾኔ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል አስረክበዋል። የውጭ ጉዳይ ቃል አቀባይ ፅህፈት ቤት ለአርትስ ቲቪ በላከው መግለጫ እንዳመለከተው  የቀዳማዊት እመቤት ጽህፈት ቤት  በገጠር አካባቢ በትምህርት ቤት ርቀት ምክንያት ትምህርት የሚያቋርጡ ተማሪዎችን ችግር ለመቅረፍ ባቅራቢያቸው ትምህርት ቤቶቹን እንደሚገነባ ገልጿል፡፡

የሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትርና የዓለም አቀፉ የፍልሰት ድርጅት የኢትዮጵያ ተጠሪ ተወያዩ

የሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ እና የዓለም አቀፉ የፍልሰት ድርጅት የኢትዮጵያ ተጠሪ ማውረን አቺንግ ጋር በሁለትዮሽ የትብብር ጉዳዮች ዙሪያ መከሩ ምክክራቸውም ዜጎች በሀገራቸው ሰርተው መለወጥ በሚችሉበት ሁኔታ፣ እንዴት በህጋዊ መንገድ ለሥራ መጓዝ እንደሚችሉ ግንዛቤ በመፍጠርና ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርን በጋራ መከላከል በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ያተኮረ መሆኑ ተገልጿል። በተጨማሪም ሕጋዊ የውጭ አገር የሥራ ስምሪትን የማጠናከር […]