loading
አዲስ ወግ ዌቢናር ለሁለተኛ ግዜ ፈጠራ በቀውስ ጊዜ በሚል ርእስ ውይይት እያደረገ ነዉ፡፡

አዲስ ወግ ዌቢናር ለሁለተኛ ግዜ ፈጠራ በቀውስ ጊዜ በሚል ርእስ ውይይት እያደረገ ነዉ፡፡ የውይይቱ ታዳሚዎች ዶክተር ታምራት ሃይሌ ከጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት፣ የቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለሰልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የታሪክ ምሁር የሆኑት ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው፣  በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና የአእምሮ ሃኪሞች የሆኑት ዶክተር ቢኒያም ወርቁ እና ዶክተር ባርኮት ሚልኪያስ ናቸው። በጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት […]

በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 ልዮ ስሙ ብርጭቆ ኮንደሚኒየም የሚገኙ ባለሀብት ኮሮና ቫይረስን ለመከላከል የሚያስችል የኬሚካል ርጭት አካሄዱ ፡፡

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 24 ፣ 2012 በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 ልዮ ስሙ ብርጭቆ ኮንደሚኒየም የሚገኙ ባለሀብት ኮሮና ቫይረስን ለመከላከል የሚያስችል የኬሚካል ርጭት አካሄዱ ፡፡ ግለሰቡ 10 ሺ አባወራዎች በሚገኙበት አካባቢ ኬሚካል ያስረጩ ሲሆን በዚህ ወቅት የራስን ጤንነት ብቻ ሳይሆን የአካባቢንና የህብረተሰብን ጤና ማስጠበቅ አስፈላጊ እንደሆነም ተናግረዋል፡፡ ኬሚካሉ የማህበረሰቡን ፍቃደኝነት በመጠየቅ እቤት ለቤት […]

ሰሜን ኮሪያ ትምህርት ቤቶችን በድጋሚ ልትከፍት ነው፡፡

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 24 ፣ 2012 ሰሜን ኮሪያ ትምህርት ቤቶችን በድጋሚ ልትከፍት ነው፡፡ ሰሜን ኮሪያ የኮቪድ 19 ወረርሽኝን ለመለከላከል ዝግ አድርጋ የቆየቻቸውን ትምህርት ቤቶችን በያዝነው የፈረንጆቹ ወር ልትከፍት መሆኑን አስታውቃለች፡፡ ፒዮንግያንግ እስከአሁን አንድም በቫይረሱ የተያዘ ሰው ሪፖርት ያላደረገች ቢሆንም ድንበሮቿን መዝጋትን ጨምሮ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎቿን በለይቶ ማቆያ እስከ መለየት የሚደርስ ጠናካራ ህጎችን ተግባራዊ […]

በጆርጅ ፍሎይድ ግድያ ምክንያት የተቀሰቀሰው ተቃውሞ ከአሜሪካ አልፎ ዓለም አቀፍ ይዘት እየተላበሰ ነው ተባለ::

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 24 ፣ 2012 በጆርጅ ፍሎይድ ግድያ ምክንያት የተቀሰቀሰው ተቃውሞ ከአሜሪካ አልፎ ዓለም አቀፍ ይዘት እየተላበሰ ነው ተባለ:: አሁን ላይ የጥቁሮች ህይዎት ያሳስበናል የሚለው ተቃውሞ ከአሜሪካ ከተሞች አልፎ በእግሊዝ፣ በጀርመን በኒው ውዚ ላንድ እና በሌሎች ሀገራትም እየተካሄደ ይገኛል፡፡ በቅርቡ በፖሊስ መኮንን የተገደለው ጥቁር አሜሪካዊ ጆርጅ ፍሎይድ ጉዳይ በኮሮናቫይረስ ለምትታመሰው አሜሪካ ሌላ ራስ […]

የጋምቤላ ክልል ከደቡብ ሱዳን ጋር በሰፊው የሚዋሰን በመሆኑ በድንበር የሚገቡ ዜጎችን ለመቆጣጠር ፈታኝ ሆንዋል ተባለ፡፡

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 24 ፣ 2012 የጋምቤላ ክልል ከደቡብ ሱዳን ጋር በሰፊው የሚዋሰን በመሆኑ በድንበር የሚገቡ ዜጎችን ለመቆጣጠር ፈታኝ ሆንዋል ተባለ፡፡ የጋምቤላ ክልል ፕሬስ ሴክሬታሪያት ጽህፈት ቤት ለአርትስ በላከዉ መግለጫ፤ ክልሉ ከደቡብ ሱዳን ጋር በሰፊው እንደሚዋሰን የጠቆሙት አቶ ኡሞድ በድንበር አካባቢ የሰዎች ዝውውርን ለመግታት እየተሰራ ቢሆንም የሚፈለገውን ያህል እንዳልሆነ ተናግረዋል፡፡ በመሆኑም የመግቢያና የመውጫ በሮች […]

የእንጦጦ ሀመረ ኖህ ኪዳነምህረት አካባቢ ተወለጆች በአካባቢያቸው ለሚገኙ  አቅመ ደካሞች  የምግብና የአይነት ድጋፍ አደረጉ::

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 24 ፣ 2012 የእንጦጦ ሀመረ ኖህ ኪዳነምህረት አካባቢ ተወለጆች በአካባቢያቸው ለሚገኙ  አቅመ ደካሞች  የምግብና የአይነት ድጋፍ አደረጉ::   የእንጦጦ ሀመረ ኖህ ኪዳነምህረት አካባቢ ተወለጆች   የኮቪድ 19 በሽታ ወረርሽኝ  የሚያስከትለውን  ችግር ለመከላከል በአካባቢያቸው ለሚገኙ  ከ 3 መቶ በላይ  ለሚሆኑ ድጋፍ ፈላጊዎች   የምግብና የአይነት ድጋፍ ማድረጋቸውን የወጣቶቹ አስታባበሪ አቶ  አሳልፈው ጌትነት   ገልፀዋል፡፡  እነዚህ ወጣቶች ለወገናቸው […]

የኮሮናቫይረስን ለመከላከል የሚጠቅሙ ተብሎ በጤና ባለሙያዎች የተለዩ ምግቦች እንደሌሉ የጤና ሚኒስቴር ገለጸ::

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 24 ፣ 2012 የኮሮናቫይረስን ለመከላከል የሚጠቅሙ ተብሎ በጤና ባለሙያዎች የተለዩ ምግቦች እንደሌሉ የጤና ሚኒስቴር ገለጸ:: የኮሮናቫይረስ (ኮቪድ-19) ወረርሽኝን ለመከላከልና ከበሽታው የሚያድኑ ተብሎ እስካሁን በጤና ባለሙያዎች ምክረ ሃሳብ ተመሥርተው የቀረቡ የተለዩ የምግብ ዓይነቶች አለመኖራቸውን የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ገለጹ።ኅብረተሰቡ አሁንም በመንግሥትና በጤና ባለሙያዎች የሚቀርቡለትን መመሪያዎች ተግባራዊ በማድረግ ከቫይረሱ ራሱንና ወገኑን መከላከል እንደሚገባው […]

ስፔን ከሶስት ወራት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በኮሮናቫይረስ ሰው ሳይሞትባት 24 ሰዓታት ተቆጥረዋል::

ስፔን ከሶስት ወራት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በኮሮናቫይረስ ሰው ሳይሞትባት 24 ሰዓታት ተቆጥረዋል:: በስፔን የኮሮናቫይረስ እንደከተሰተ የመጀመሪያው ሞት በፈረንጆቹ ማርች 3 ቀን ነበር የተመዘገበው፡፡ቀስበቀስ የበሽታው ስርጭት እየተስፋፋ መጥቶ ስፔን በርካታ ዜጎቿን በቫይረሱ ምክንያት አጥታለች፡፡ አልጀዚራ በዘገባው እንዳስነበበው በሀገሪቱ ታሪክ በ24 ሰዓታት ውስጥ በጣም ከፍተኛው የሞት መጠን 950 ሆኖ ተመዝግቧል፡፡ የሀገሪቱ የአስቸኳይ የጤና ጉዳዮች ምላሽ ሀላፊ ፌርናንዶ […]

ለኮሮና ቫይረስ መከላከል ድጋፍ የሚውል ከ500 ሺህ በላይ ማስክና የገንዘብ ድጋፍ ተበረከተ።

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 25፣ 2012 ለኮሮና ቫይረስ መከላከል ድጋፍ የሚውል ከ500 ሺህ በላይ ማስክና የገንዘብ ድጋፍ ተበረከተ። በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ከ6 የቻይና ተቋማት የተሰባሰቡ 500 ሺህ ማስኮችና የተለያዩ ቁሳቁሶችን ለከተማ አስተዳደሩ አበርክተዋል። የተለያዩ ኢትዮጵያውያን ተቋማትም 1ነጥብ 1 ሚሊየን ብር ድጋፍ ያደረጉ ሲሆን በተጨማሪም 180 ሺህ ብር የሚገመት በእግር የሚሰራ እጅ መታጠቢያ ድጋፍ ተደርጓል። ድጋፉን የተረከቡት […]

በኢትዮጵያ የኮሮናቫይረስ መመርመሪያ ማዕከላት ቁጥር 46 ደረሰ፡፡

በኢትዮጵያ የኮሮናቫይረስ መመርመሪያ ማዕከላት ቁጥር 46 ደረሰ፡፡የጤና ሚኒስቴር በፌስቡክ ገጹ እንዳስታወቀዉ የኮሮና ቫይረስ ኢትዮጵያ መግባቱ ሲረጋገጥ ምንም ዓይነት የመመርመሪያ ማዕከል ያልነበራት ኢትዮጵያ በአሁን ወቅት 46 ማዕከላት አላት ብሏል፡፡የጤና ሚኒስቴር ይህን ችግር በመረዳት በአጭር ጊዜ በአገር ውስጥ የመመርመሪያ መሳሪዎችን በሟሟላት እና ባለሙያዎችን በማሰልጠን የላብራቶሪ ምርመራ ማዕከላትን አደራጅቷል፡፡ የሚኒስቴሩ የመመርመር አቅም ከጊዜ ወደጊዜ እየጨመረ እንደመጣም ገልጿል፡፡እስከ ግንቦት […]