loading
ህዳሴው ግድብ ላይ የሚደረገው ድርድርድር ከቴክኒክ አንፃር መሰረታዊ የተባሉ ጉዳዮች ቢፈቱም ሙሉ ስምምነት ሆኖ ለመውጣት የሚቀረው ጉዳይ እንዳለ ተገለፀ::

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 11 ፣ 2012 ህዳሴው ግድብ ላይ የሚደረገው ድርድርድር ከቴክኒክ አንፃር መሰረታዊ የተባሉ ጉዳዮች ቢፈቱም ሙሉ ስምምነት ሆኖ ለመውጣት የሚቀረው ጉዳይ እንዳለ ተገለፀ:: በመጀመርያ የውሃ ሙሌትና አመታዊ ስራ ላይ ትኩረቱን አድርጎ በኢትዮጵያ በሱዳንና ግብፅ መካከል በቪዲዮ በመታገዝ እየተካሄደ ያለው ድርድር ለሰባተኛ ቀን ትላንት ተካሂዷል።የኢፌዴሪ የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር እንዳለው ከሚኒስትሮቹ ውይይት ቀደም […]

በኮሮና ዙርያ የተሰሩ ከ20 በላይ ጥናቶች በኦን ላይን ኮንፈረንስ ለውይይት በመቅረብ ላይ ናቸው ።

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 11 ፣ 2012 በኮሮና ዙርያ የተሰሩ ከ20 በላይ ጥናቶች በኦን ላይን ኮንፈረንስ ለውይይት በመቅረብ ላይ ናቸው ።የኦንላይን ኮንፍረንሱ ምሁራን በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ዙሪያ ያከናወኑዋቸው ጥናቶች ለማሳወቅና ቫይረሱን አስመልክቶ የእውቀት ሽግግር ለማድረግ ያለመ ነው ብለዋል።ውይይቱ ላይ የመቐለ አዲስ አበባ ፣ ባህርዳር እና ሃረማያ ዩኒቨርሲቲዎች ምሁራን የተሳተፉበት መሆኑን ዶክተር አዲሱ ተናግረዋል ።ጥናታዊ ጽሁፎቹ […]

በአፍሪካ ህብረት የፓን አፍሪካ የእንስሳት ክትባት ማዕከል የኮሮቫይረስን ለመከላከል የሚያደርገውን የምርምር ስራ እንደሚደግፍ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ገለጸ።

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 11 ፣ 2012 በአፍሪካ ህብረት የፓን አፍሪካ የእንስሳት ክትባት ማዕከል የኮሮቫይረስን ለመከላከል የሚያደርገውን የምርምር ስራ እንደሚደግፍ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ገለጸ።የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶክተር አብርሃም በላይ በቢሾፍቱ ከተማ የሚገኙትን የአፍሪካ ህብረት የፓን አፍሪካ የእንስሳት ክትባት ማዕከልና ብሄራዊ የእንስሳት ህክምና ኢንስቲትዩት ዛሬ ጎብኝተዋል።የፓን አፍሪካ የእንስሳት ክትባት ማዕከል በክትባትና መድሃኒት ምርቶች ላይ የሚደረገውን ቁጥጥርና […]

በኮሮና ቫይረስ ምክንያት የሚከሰትን የደም አቅርቦት እጥረት ለመቅረፍ የምስራቅ ወለጋ ዞን አመራሮች ደም ለገሱ፡፡

የዞኑ ኮሚኒኬሽን ለአርትስ በላከዉ መግለጫ እንዳስታወቀዉ ቀደም ሲል የጤና ሚኒስቴርና የኢትዮጵያ ብሔራዊ የደም ባንክ አገልግሎት በኮሮና ቫይረስ ምክንያት አገራዊ የደም አቅርቦት በመቀነሱ የልገሳ ጥሪ ማቅረቡን ተከትሎ ነዉ ፡፡ በልገሳ መረሓ ግብሩ የተገኙት የምስራቅ ወለጋ ዞን አስተዳዳሪ አቶ አስመራ ኢጃራ በሰጡት አስተያየት፤ የኮሮናቫይረስ ከመግባቱ በፊት ሲቀርብ የነበረው ደም በመቀነሱ በችግር ጊዜ ሕዝብና አገርን የማሻገር ሃላፊነታችንን እንወጣለን […]

የተባበሩት መንገስታት ድርጅት ባለፈው ዓመት ብቻ በዓለም 80 ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች ከመኖሪያቸው ተፈናቅለዋል አለ

የድርጅቱ የስደተኞች ጉዳይ ቢሮ በዓመታዊ ሪፖርቱ ይፋ እንዳደረገው የመፈናቀላቸው መንስኤዎች የርስበርስ ግጭት፣ ጥቃት፣ የሰብዓዊ መብት ጥሰት እና ተያያዥ ችግሮች ናቸው፡፡ አልጀዚራ በዘገባው እንዳስነበበው 79.5 ሚሊዮን ከሚሆኑት ተፈናቃዮች መካከል 26 ሚሊዮን ስደተኞች፣ 4.2 ሚሊዮን ጥገኝነት ጠያቂዎች፣ ከ45 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት ደግሞ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች ናቸው፡፡ በየዓመቱ የሥደተኞች ቁጥር እየጨመረ መሆኑ ያሳሰበው ድርጅቱ በተለይ በየጊዜው የሚከሰቱ ግጭቶች […]

የደቡብ ክልልና አዲሱ የሲዳማ ክልል የስልጣን ርክክብ አካሄዱ

የደቡብ ክልል እና አዲሱ የሲዳማ ክልል በደቡብ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልል ምክር ቤት ፊት ቀርበው የስልጣን ርክክብ አካሄዱ። የደቡብ ብሄሮች ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልል ምክር ቤት 5ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 2ኛ አስቸኳይ ጉባኤ የሲዳማ ዞን በክልል እንዲደራጅ በዛሬው እለት ወስኗል። ምክር ቤቱ እያካሄደ ባለው አስቸኳይ ጉባኤ የሲዳማ ዞን በክልል እንዲደራጅ የወሰነው የሥልጣን ርክብክብ እንዲደረግ […]

የአሜሪካ ማዕከላዊ ባንክ የሥራ አጦች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱ እንዳሳሰበው ገለፀ

ባለፈዉ ሳምንት ብቻአንድ ነጥብ አምስት አሜሪካዊያን የስራ አጥነት ፎርም መሙላታቸው ኮቪድ 19 በሀገሪቱ ጫናውን እንደቀጠለ መሆኑን ያመላክታል ተብሏል፡፡ ቢቢሲ እንደዘገበው በአሜሪካ ለ13 ተከታታይ ሳምንታት የሥራ አጦች ቁጥር ከ1 ሚሊዮን በላይ እየሆነ መመዝገቡ ተስተውሏል፡፡ ይህን ያስተዋለው የሀገሪቱ ማእከላዊ ባንክ አስቸኳይ የኢኮኖሚ ማስተካከያ ካልተደረገ ችግሩ ከዚህም የከፋ ሊሆን እንደሚችል አስጠንቅቋል፡፡ ምንም እንኳ አሜሪካ በኮሮናቫይረስ ምክንያት ተዘግተው የነበሩ […]

የኮቪድ19 ወረርሽኝን ለመግታት የቻይና አፍሪካ ትብብር የማይተካ ሚና አለው አሉ አቶ ገዱ አንዳርጋቸው

የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽ/ቤት ለአርትስ በላከዉ መግለጫ  እንዳስታወቀዉ የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው በዓለም ላይ የተከሰተውን የኮቪድ19 ወረርሽኝ ለመግታት የቻይና አፍሪካ ትብብር የማይተካ ሚና አለዉ ብለዋል የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ትናንት “ዓለም አቀፉ የአንድ ቀበቶ አንድ መንገድ ኢኒሸቲቭ” የቪዲዮ ኮንፈረንስ በተካሄገበት ወቅት እንዳሉት ፤የዓለም ስጋት የሆነውን የኮቪድ19 ወረርሽኝ ለመግታት በቻይና እና አፍሪካ መካከል የሚደረገው ትብብር ከምንጊዜውም በላይ ወሳኝ ነዉ። ቻይና የኮቪድ19 ወረርሽኝን ለመግታት የተከተለችውን ስትራቴጂ እና የተገኘውን ውጤትም አድንቀዋል። ኢትዮጵያ የኮቪድ19 ወረርሽኝን ለመግታት እያደረገች ባለው እንቅስቃሴ የቻይና መንግስት እና እንደ ጃክማ የመሳሰሉ የቻይና በለሃብቶች እያደረጉት ላለው ድጋፍ ያመሰገኑት አቶ ገዱ፥ ድጋፉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ያላቸውን እምነት ገልጸዋል። በኮንፈረንሱ ላይ የቻይና ስቴት ካውንስልና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ይን ጨምሮ የተለያዩ ሃገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች፣ የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ቴዎድሮስ አድሃኖም፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅትና ሌሎች ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ተወካዮች ተሳትፈዋል። “የአንድ ቀበቶ አንድ መንገድ ኢኒሸቲቭ” ዓለም አቀፍ ትብብርን በማሳደግ የኮቪድ19 ወረርሽኝን ለመግታት የሚያስገኘውን ጠቀሜታ በተመለከተ በስፋት መብራራቱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ፅህፈት ቤት የላከልን መግለጫ  ያመለክታል።

ኬንያ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ተለዋጭ አባልነት ምርጫን አሸነፈች

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 12 ፣ 2012  ቢቢሲ እንደዘገበው ከአፍሪካ ሀገራት ኬንያ እና ጂቡቲ በተወዳሩበት ምርጫ ኬንያ ጂቡቲን 129 ለ62 በሆነ የድምፅ ልዩነት በማሸነፍ ነው የምክር ቤቱን መቀመጫ ያገኘችው፡፡የኬንያው ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ጂቡቲን በብርቱ ተፎካካሪነቷ አድንቀው የአፍሪካ ህብረትን ደግሞ ለሀገራቸው ለሰጠው እውቅና አመስግነዋል፡፡ኬንያ ይህን ውድድር ማሸነፏ በአካባቢው ያላት ተሰሚነት ከፍ እያለ የመምጣቱን የሚያመላክት ነው ያሉት […]

በኢትዮጵያ የህክምና ባለሙያዎች በሚያዙት መሰረት ዴክሳሜታዞን ለኮቪድ 19 ህሙማን እንደ ድንገተኛ ህክምና ለመጠቀም ተወሰነ ።

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 12 ፣ 2012  በኢትዮጵያ የህክምና ባለሙያዎች በሚያዙት መሰረት ዴክሳሜታዞን ለኮቪድ 19 ህሙማን እንደ ድንገተኛ ህክምና ለመጠቀም ተወሰነ ።የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ እንዳስታወቁት ;ለኮቪድ-19 ህሙማን የሚውለውን ዴክሳሜታዞን የተባለውን መድሀኒት በተመለከተ በእንግሊዝ መንግስት የተካሄደውን ጥናት እና ሪፖርት በዝርዝር ተመልክተነዋል ብለዋል፡፡የህክምና ጉዳዮች አማካሪ ቡድናችን እና የጤና ባለሙያዎች አማካሪ ምክር ቤት፣ የሰጠንን ምክረ ሀሳብ […]