loading
አዲሱ ተገኘ የተባለው የኮሮና ቫይረስ ዝርያ ለዓለም ሀገራት ስጋት እየሆነ ነው ተባለ ::

አዲስ አበባ፣ታህሳስ 13፣ 2013 አዲሱ ተገኘ የተባለው የኮሮና ቫይረስ ዝርያ ለዓለም ሀገራት ስጋት እየሆነ ነው ተባለ :: በዚህም አዲሱ ቫይረስ በመጀመሪያ  ታይቷል ከተባለበት ከእንግሊዝ ወደ ተለያዩ አገራት የሚደረጉ በረራዎችን ታግደዋል። የአውሮፓ ሕብረት አባል አገራት በዚህ ዙሪያ የጋራ ፖሊሲ ለማውጣት እየተወያዩ ነው የተባለው፡፡ ሲሆን ዴንማርክ ውስጥም አዲሱ የቫይረስ ዝርያ በመታየቱ ስዊድን ወደ ዴንማርክ የሚደ ረገዉንም ጉዞ አግዳለች። የወረርሽኙ […]

ኢጋድ በሬይክ ማቻር ላይ ጥሎት የነበረውን የጉዞ እገዳ አነሳ::

አዲስ አበባ፣ታህሳስ 13፣ 2013 ኢጋድ በሬይክ ማቻር ላይ ጥሎት የነበረውን የጉዞ እገዳ አነሳ:: የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት (ኢጋድ) በደቡብ ሱዳን የእርስ በእርስ ጦርነት ወቅት በተቀናቃኝ መሪው ሬይክ ማቻር ላይ ጥሎት የነበረውን የጉዞ እገዳ ሙሉ በሙሉ አነሳ፡፡ እገዳው የተነሳው ጦርነቱ ቆሞ ተቀናቃኝ አካላቱ ከስምምነት ላይ ደርሰው በጋራ መስራት በመጀመራቸው ነው፡፡ በዚህም ማቻር የቀጣናዊው ተቋም  አባል ወደሆኑ […]

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ፓርቲዎች ማሟላት የሚገባቸዉን ግዴታዎች ያላሟሉ ፓረቴዎች ላይ እርምጃ መዉሰዱን አስታዉቋል፡፡

አዲስ አበባ፣ታህሳስ 14፣ 2013 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ፓርቲዎች ማሟላት የሚገባቸዉን ግዴታዎች ያላሟሉ ፓረቴዎች ላይ እርምጃ መዉሰዱን አስታዉቋል፡፡ በዚህም 26 ፓረቲዎች በቦርዱ ሚጠበቅባቸዉን ባለማሟላታቸዉ መሰረዛቸዉ ታዉቋል፡፡ ሁሉም ፓለቲካ ፓርቲዎች ማሟላት ያለባቸውን መስፈርቶች በጽሁፍ እንዲደርሳቸው እንዲሁም ማምጣት ያለባቸውን ተጨማሪ የመስራች ፊርማ ቁጥር በመጥቀስ እንዲያቀርቡ ተጠይቀዋል፡፡ በዚህም መሰረት ማሟላት ያለባቸውን ሰነዶች ያላቀረቡ 26 ፓርቲዎች ተሰርዘዋል ብሏል :: […]

ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ በአምስት ወር ዉስጥ ከ18 ሺህ በላይ የወንጀል መዛግብት ውሳኔ ሰጥቼያለሁ አለ፡፡

አዲስ አበባ፣ታህሳስ 14፣ 2013 ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ በአምስት ወር ዉስጥ ከ18 ሺህ በላይ የወንጀል መዛግብት ውሳኔ ሰጥቼያለሁ አለ፡፡ በጠቅላይ ዐቃቤ ህግ የፕሬስ ሴክሪታሪያት ኃላፊ አወል ሱልጣን እንደገለጹት የወንጀል ፍትህ አስተዳደር ስርዓቱን ቀልጣፋና ውጤታማ በማድረግ፣ የፍትህ ስርዓትን በማስፈን እና ወንጀለኞችን ለህግ በማቅረብ ረገድ ተቋሙ በርካታ ስራዎችን መስራት ችሏል ብለዋል፡፡ በዚሁም መሰረት በአምስት ወር አፈጻጸም ውስጥ በሁሉም […]

እስራኤል በሁለት ዓመት ውስጥ አራተኛ ምርጫ ማካሄዷ የግድ ሆኖባታል ተባለ::

አዲስ አበባ፣ታህሳስ 14፣ 2013 እስራኤል በሁለት ዓመት ውስጥ አራተኛ ምርጫ ማካሄዷ የግድ ሆኖባታል ተባለ:: የጠቅላይ ሚንስትር ቤናሚን ኔታኒያሁና የአጣማሪያቸው ቤኒ ጋንትዝ የአንድነት መንግስት በገጠመው ፖለቲካዊ አለመረጋጋት ድንገቴ ምርጫ የማካሄድ ግዴታ ውስጥ ገብቷል፡፡ ባለፉት ሳምንታት የሀገሪቱ ምክር ቤት ፈርሶ አዲስ ምርጫ ይካሄድ የሚል ሀሳብ በህግ አውጭ አባላት መቅረቡን ተከትሎ ፓርላማው ፈርሷል ነው የተባለው፡፡ አልጀዚራ እንደዘገበው ምርጫው […]

በእንግሊዝና ፈረንሳይ መካከል ተጥሎ የነበረው የጉዞ እገዳ መነሳቱን ተከትሎ የትራንስፖርት አገልግሎቱ ዳግም ተጀምሯል፡፡

አዲስ አበባ፣ታህሳስ 14፣ 2013 በእንግሊዝና ፈረንሳይ መካከል ተጥሎ የነበረው የጉዞ እገዳ መነሳቱን ተከትሎ የትራንስፖርት አገልግሎቱ ዳግም ተጀምሯል፡፡ በእንግሊዝ አዲሱ የኮሮናቫይረስ በመከሰቱ በርካታ ሀገራት የጉዞ እቀባ መጣላቸውን የሚታወስ ሲሆን ፈረንሳይም አንዷ እንደነበር አይዘነጋም፡፡ አሁን ላይ ሀገራቱ በደረሱት ስምምነት መሰረት በእንግሊዝና ፈረንሳይ መካከል የሚደረጉ የባቡር ፣የአየርና የባህር ጉዞዎች ዳግም እንደሚጀመሩ ነው የተነገረው፡፡ የፈረንሳይ ዜጎችና በፈረንሳይ የሚኖሩ የእንግሊዝ […]

በመተከል ያለዉን የፀጥታ ችግር ከመሰረቱ ለመፍታት የተቀናጀ ኃይል እንዲሰማራ መደረጉን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ገለጹ፡፡

አዲስ አበባ፣ታህሳስ 15፣ 2013 በመተከል ያለዉን የፀጥታ ችግር ከመሰረቱ ለመፍታት የተቀናጀ ኃይል እንዲሰማራ መደረጉን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቤንሻንጉል ክልል በመተከል ዞን ያለዉ የጸጥታ ችግር በተለያየ መንገድ ለመፍታት የተቀናጀ ኃይል እንደሰማራ ተደርጓል ብለዋል፡፡ በቤንሻንጉል ክልል መተከል ዞን በዜጎች ላይ እየተፈፀመ ያለዉ ጭፍጨፋ እጅግ ኣሳዛኝ መሆኑን ጠቅላየሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡ በወገኖቻችን ላይ በተፈጸመዉ ኢሰባዊ ድርጊትም […]

በጋራ የድንበር አካባቢ በሱዳን በኩል የተደረጉ አዳዲስ ለዉጦችን የቀደሙ ስምምነቶችን የሚጥሱ በመሆናቸዉ በአስቸኳይ እንዲቆሙ ኢትዮጵያ አሳሰበች::

አዲስ አበባ፣ታህሳስ 15፣ 2013 በጋራ የድንበር አካባቢ በሱዳን በኩል የተደረጉ አዳዲስ ለዉጦችን የቀደሙ ስምምነቶችን የሚጥሱ በመሆናቸዉ በአስቸኳይ እንዲቆሙ ኢትዮጵያ አሳሰበች:: የጠቅላይ ሚኒስቴር ፕሬስ ሰክሬተርያት ጽ/ቤት ለአርትስ በላከዉ መረጃ እንዳስታወቀዉ፤ ሱዳን ከጥቅምት ወር መጨረሻ ጀምሮ ድንበር አካባቢ የቀደሙ ስምምነቶችን የሚጥሱ ፤እና መሬት ላይ ያለዉን እዉነታ የሚለዉጡ እንቅስቃሴዎችን እያደረገች እንደሆነና እንቅስቃሴዉ በአስቸኳይ እንደቆምና ወደቀደመዉ ቦታ እንዲመለስ የኢትዮጵያ […]

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሁለት ፓርቲዎችን ፈቃድ ሰረዘ፡፡

አዲስ አበባ፣ታህሳስ 20፣ 2013 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሁለት ፓርቲዎችን ፈቃድ ሰረዘ፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በታህሳስ 13 ቀን 2013 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ መሰረት ማሟላት ያለባቸው መስፈርቶች እንዲያሟሉ ከተጠየቁት መካከል አራት ፓርቲዎች መስፈርቱን ያሟሉ ሲሆን ሁለት ፓርቲዎች ደግሞ ባለሟሟላታቸው መሰረዛቸውን ገልጿል፡፡ የተጠየቀውን መስፈርት ያሟሉ ፓርቲዎች ፤የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር /ኦብነግ/- የአፋር ሕዝብ ፓርቲ /አሕፓ/፤ የጋሞ […]

በዳያስፖራው የተፈጠረው መነሳሳትና የአንድነት ስሜት ቀጣይነት እንዲኖረው ጥረት እየተደረገ ነው ተባለ::

አዲስ አበባ፣ታህሳስ 20፣ 2013 በዳያስፖራው የተፈጠረው መነሳሳትና የአንድነት ስሜት ቀጣይነት እንዲኖረው ጥረት እየተደረገ ነው ተባለ:: የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ኤጀንሲ እንዳስታወቀዉ የዳያስፖራዉ ማህበረሰብ በሀገር ልማትና ዕድገት ለማሳተፍ የሚያስችሉ ሥራዎች እየተሠሩ እንደሆነ ገልጿል፡፡ የዳያስፖራ የምክክር መድረክ በደቡብ አፍሪካ በተካሄደበት ወቅት የኤጀንሲዉ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሠላማዊት ዳዊት እንዳሉት ዳያስፖራው አባላት በንግድና ኢንስትመንት፣ በዕውቀት ሽግግር፣ በሬሚታንስና በሌሎች ወሳኝ የሀገር ልማት […]