loading
በደቡብ አፍሪካ የስደተኛ ጠልነት ችግር አሁንም የማይጠፋ አዙሪት ሆኖ ቀጥሏል ተባለ::

አዲስ አበባ፣ መስከረም 8፣ 2013  በደቡብ አፍሪካ የስደተኛ ጠልነት ችግር አሁንም የማይጠፋ አዙሪት ሆኖ ቀጥሏል ተባለ:: በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ የውጭ ሀገር ዜጎች በሀገሬው ተወላጆች የሚደርስባቸው ጥቃት ተባብሶ መቀጠሉ እንዳሳሰበው ሂውማን ራይትስ ዋች የተባለው የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ተቋም ገልጿል፡፡ ድርጅቱ ከአፍሪካ እና ከእስያ ተሰደው በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ ሰዎች በየትኛውም ጊዜ የመጤ ጠሎቹ ኢላማዎች መሆናቸውን አረጋግጫለሁ ብሏል፡፡ […]

በአውሮፓ የኮሮናቫይረስ ስርጭት መጨመሩ እንዳሳሰበው የዓለም ጤና ድርጅት ገለፀ::

አዲስ አበባ፣ መስከረም 8፣ 2013  በአውሮፓ የኮሮናቫይረስ ስርጭት መጨመሩ እንዳሳሰበው የዓለም ጤና ድርጅት ገለፀ:: ድርጅቱ በሪፖርቱ ይፋ እንዳደረገው በአውሮፓ በሳምንት ውስጥ የበሽታው ስርጭት በማርች ወር ከተመዘገበው ከፍተኛ ቁጥር የበለጠ ሆኖ ተመዝግቧል፡፡ በዓለም ጤና ድርጅት የአውሮፓ አህጉር ሪጂናልን ዳይሬክተር የሆኑት ዶክተር ሃንስ ክሉግ አሁን ላይ በአህጉሩ እየታየ ያለው የቫይረሱ ስርጭት አሳሳቢ ደረጃ ላይ ነው ብለዋል፡፡ በአወሮፓ […]

ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ዳግም ትመህርት ለማስጀመር የሚያስችል ጉባዔ በጂማ ዩኒቨርሲቲ መካሄድ ጀመረ ::

አዲስ አበባ፣ መስከረም 11፣ 2013 ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ዳግም ትመህርት ለማስጀመር የሚያስችል ጉባዔ በጂማ ዩኒቨርሲቲ መካሄድ ጀመረ ::ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ዳግም ትመህርት ማስጀመር የሚቻልበት ሁኔታ ላይ የሚመክር ጉባዔ በጂማ ዩኒቨርሲቲ ተጀምሯል። በጉባኤው ላይ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴርና የጤና ሚኒስቴር የስራ ሃላፊዎች፣ የዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንቶችና ሌሎች የሚመለከታቸዉ አካላት ተገኘተዋል።በጉባኤው ዩኒቨርሲቲዎች የኮሮናቫይረስ (ኮቪድ-19) ወረርሽኝ ከተከሰተ ጀምሮ ወረርሽኙን ለመከላከል […]

በእንግሊዝ የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ከፍተኛ ደረጃ መድረሱን የሀገሪቱ የጤና ሃላፊ አስታወቁ፡፡

አዲስ አበባ፣ መስከረም 11፣ 2013 በእንግሊዝ የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ከፍተኛ ደረጃ መድረሱን የሀገሪቱ የጤና ሃላፊ አስታወቁ፡፡የእንግሊዝ ጤና ሃላፊ ማት ሃንኮክ የኮሮናቫይረስ ስርጭት ከፍተኛ ጫፍ ላይ መድረሱን የተናገሩ ሲሆን የቫይረሱን ስርጭት ለመግታት ተጨማሪ ክልከላዎች ሊተገበሩ ይገባል ብለዋል፡፡አሁን ላይ ያለን ምርጫ ክልከላዎችን በማያከብሩ ሰዎች ላይ እርምጃ መውሰድ መጀመር አለብን ብለዋል ዋና ፀሐፊው፡፡ በመንግስት በኩል የተቀመጡ የጥንቃቄ እርምጃዎችንና ክልከላዎችን […]

የኮትዲቯር ህዝባዊ አመፅ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 11፣ 2013  የኮትዲቯር ተቃዋወች በፕሬዚዳንት አላሳኒ ኦታራ ላይ ህዝባዊ አመፅ እንዲቀሰቀስ ጥሪ አስተላለፈፉ::የተቃውሞው መነሻ እንደ አውሮፓዊያኑ አቆጣጠር በ2010 ወደ ስልጣን የመጡት ኦታራ በ2015 ዳግም ተመርጠው ሀገሪቱን እያስተዳደሩ የሚገኙ ሲሆን አሁን ለሶስተኛ ጊዜ እወዳደራለሁ ማለታቸውን ህገ መንግስቱ አይፈቅድላቸውም የሚል ነው፡፡ በሀገሪቱ የብዙ ተቃዋሚ ፓርቲወች ስብስብና ዋነኛ የምርጫው ተቀናቃኝ ሆኖ የቀረበው ፓርቲ የኦታራ እንቅስቃሴ […]

ብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ለፀጥታና ደህንነት አካላት የፀረ-ሽብር ሥልጠና ሰጠ::

አዲስ አበባ፣ መስከረም 13፣ 2013ብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ለፀጥታና ደህንነት አካላት የፀረ-ሽብር ሥልጠና ሰጠ::ብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ለፀጥታና ደህንነት አካላት ሽብርተኝነትን መከላከልና ማክሸፍ በሚያስችሉ ስልቶች ላይ ያጠነጠነ ስልጠና መስጠቱን ገልጿል። ስልጠናው ከመከላከያ ሠራዊት፣ ከብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት፣ ከፌዴራልና ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽኖች፣ ከሪፐብሊካን ጋርድና ከኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ልዩ ኃይል ለተውጣጡ አመራሮችና አባላት ነው የተሰጠው።ሽብርተኝነትን መከላከልና […]

የኢራን ፕሬዚዳንት አሜሪካ በምታደርገው ምርጫ ሀገራቸው መደራደሪያ ሆና አትቀርብም አሉ ፡፡

አዲስ አበባ፣ መስከረም 13፣ 2013 የኢራን ፕሬዚዳንት አሜሪካ በምታደርገው ምርጫ ሀገራቸው መደራደሪያ ሆና አትቀርብም አሉ ፡፡የኢራኑ ፕሬዚዳንት ሃሰን ሮሃኒ በቨርቹዋል በተካሄደው 75ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር ኢራን በአሜሪካ ምርጫም ሆነ በውስጥ ጉዳይ ላይ በጭራሽ መደራደሪያ ሆና አትቀርብም ብለዋል፡፡ ፕሬዚዳንቱ በንግግራቸው የሀገራችን ክብርና ብልጽግና ከምንም ነገር በላይ አስፈላጊያችን ነው ያሉ ሲሆን […]

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ላደረጉ ዓለም አቀፍ ተቋማትና ዲፕሎማቶች በ”ገበታ ለሀገር” ፕሮጀክቶች ዙሪያ ማብራሪያ ሰጥቶ ነበር፡፡

አዲስ አበባ፣ መስከረም 13፣ 2013 የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ላደረጉ ዓለም አቀፍ ተቋማትና ዲፕሎማቶች በ”ገበታ ለሀገር” ፕሮጀክቶች ዙሪያ ማብራሪያ ሰጥቶ ነበር፡፡የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ የጀመረችው የ”ገበታ ለሀገር” መርሃ ግብር የሸገር ፕሮጀክት ተከታይ ምዕራፍ ነው። በኢትዮጵያ ጎርጎራ፣ ኮይሻና ወንጪ የሚገነቡት “የገበታ ለሀገር” ፕሮጀክቶች የአረንጓዴ ኢኮኖሚን ለማሳደግ የሚያግዙ መሆናቸውን ገልጸዋል።በመሆኑን ዓለም […]

በሞዛምቢክ እየተባባሰ የመጣው የሽብር ጥቃት በመቶ ሽዎች የሚቆጠሩ ዜጎችን ለስደት ዳርጓል ተባለ::

አዲስ አበባ፣ መስከረም 13፣ 2013 በሞዛምቢክ እየተባባሰ የመጣው የሽብር ጥቃት በመቶ ሽዎች የሚቆጠሩ ዜጎችን ለስደት ዳርጓል ተባለ:: በሀገሪቱ በምንግስት ወታደሮች እና ነፍጥ አንግበው ጥቃት በሚያደርሱ ታጣቂዎች መካከል የሚደረገው ውጊያ በርካታ ዜጎችን የእንግልትና የስቃይ ሰለባ አድርጓቸዋል ነው የተባለው፡፡ አፍሪካ ኒውስ እንደዘገበው በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሞዛምቢክ ካቦ ዴልጋዶ በተባለው አካባቢ ታጣቂዎቹ የሚያደርሱት ጥቃት ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ በዚህም […]

በአዲስ አበባ የሚገኙ 26 የግል የትምህርት ተቋማት የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ባስከተለባቸው የኢኮኖሚ ጫና የሙያ ፈቃዳቸውን መለሱ።

አዲስ አበባ፣ መስከረም 13፣ 2013 በአዲስ አበባ የሚገኙ 26 የግል የትምህርት ተቋማት የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ባስከተለባቸው የኢኮኖሚ ጫና የሙያ ፈቃዳቸውን መለሱ።የከተማ አስተዳደሩ የትምህርትና ስልጠና ጥራት ሙያ ብቃት ምዘና ማረጋገጫ ባለስልጣን እንዳስታወቀዉ  ከእነዚህ መካከል 11 መዋዕለ ህጻናት፤ 13 የአንደኛ ደረጃና ሁለቱ ደግሞ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ናቸዉ፡፡ 670 የግል የትምህርት ተቋማት ደግሞ የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ማግኘታቸውም ተገለጿል።የባለስልጣኑ […]