loading
“ፈጠራ በቀውስ ጊዜ” የአዲስ ወግ ዌቢነር ውይይት በቪዲዮ ኮንፈረንስ ተካሄደ::

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 20፣ 2012 “ፈጠራ በቀውስ ጊዜ” የአዲስ ወግ ዌቢነር ውይይት በቪዲዮ ኮንፈረንስ ተካሄደ:: በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አዘጋጅነት በተካሄደዉ ዉይይት  በቀውስ ጊዜ የሚፈጠሩ አዳዲስ ችግሮችን ማለፍ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ አተኩሯል፡፡ችግር ለፈጠራ መንስኤ በመሆኑ ችግር ፈቺ ፈጠራዎች ላይ ትኩረት ሊደረግ እንደሚገባ የቪዲዮ ኮንፈረንሱ አወያይ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ ዶክተር አብርሃም በላይ ተናግረዋል።ሁሉም ስብሰባዎች በቪዲዮ ኮንፈርንስ እንዲደረጉ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሩ፤ ውይይቶች በቪዲዮ ኮንፈረንስ አማካይነት እየተካሄዱና በቀጣይ የበለጠ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የሚደረግ መሆኑን አመልክተዋል። ኢትዮጵያ ወደ ዲጂታል ኢኮኖሚ እንድትሸጋገር የሚያግዙ የፖሊሲና የህግ ማዕቀፍ እንዲጸድቅ እየተሰራ እንደሆነም ጠቁመዋል።የኢ-ኮሜርስ፣ ኢ-ሰርቪስ፣ የኢ፤ትራንዛክሽን አዋጅ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ጸድቆ ለህዝብ ተወካዮች መላኩንም ተናግረዋል።እነዚህን አገልግሎቶች በፍጥነት ስራ ላይ ለማዋል እየተሰራ ሲሆን ከ30 በላይ በቴክኖሎጂ ላይ የሚሰሩ ተቋማት ያላቸውን የቴክኖሎጂናአማራጭ እንዲያቀርቡ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።የመንግስት ተቋማትን እናአገልግሎት ፤ሰዎች በያሉበት ሆነው ለማግኘት እንዲችሉ “የኢ-ሰርቪስ” አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል ስራ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።የኮሮናቫይረስን ለመከላከል የሚያስችል የፈጠራ ስራ እየሰሩ ያሉ ሰዎች ለሚኒስቴሩ እንዲያቀርቡ እና እውቅና እንዲያገኙ ሁኔታዎች መመቻቸቱንም ጠቁመዋል።

 ባለስልጣኑ  ሰባት መንገዶችን በአስፓልት ደረጃ ለመገንባት የሚያስችል የውል ስምምነት አካሔደ።

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 20፣ 2012 ባለስልጣኑ  ሰባት መንገዶችን በአስፓልት ደረጃ ለመገንባት የሚያስችል የውል ስምምነት አካሔደ። የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን ከ11 ነጥብ ስድስት ቢሊየን ብር በላይ በሆነ ወጭ ሰባት መንገዶችን በአስፓልት ደረጃ ለመገንባት የሚያስችል የውል ስምምነት ማከሄዱን የትራንስፖርት ሚኒስቴር አስታዉቋል፡፡የውል ስምምነት የተፈረመላቸው ሰባት መንገዶች በጥቅሉ ከ500 ኪ.ሜ በላይ ርዝመት አላቸው።ለግንባታቸው የሚውለው ገንዘብ ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያ መንግሥት የሚሸፈን መሆኑ […]

በዲሞክራቲክ ኮንጎ ለአራት ቀናት በተካሄደ የእርስ በርስ ግጭት 43 ሰዎች መሞታቸው ተነገረ፡፡

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 20፣ 2012 በዲሞክራቲክ ኮንጎ ለአራት ቀናት በተካሄደ የእርስ በርስ ግጭት 43 ሰዎች መሞታቸው ተነገረ፡፡አጃንስ ፍራንስ ፕረስ የወታደር ባለስልጣናትን ምንጭ ጠቅሶ እንደዘገበው በሀገሪቱ ምስራቃዊ ክፍል በሚገኙ ሁለት ግዛቶች በተፈጠረ ግጭት 43 ሰዎች ህይወታቸውን አጥተዋል፡፡በግጭቱ አርብ እለት ጥቃት አድራሾች ስለትና የጦር መሳሪያ በመጠቀም 21 ንጹሃን ሰዎችን መግደላቸውን ነው አጃንስ ፍራንስ ፕረስ የዘገበው፡፡ በድንበር አቅራቢያ […]

ኮቪድ19 ምርጫን ማራዘም እና “ የህግ አማራጮች” በሚል ርዕስ ውይይት ተካሄደ::

አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 21 ፣ 2012 ኮቪድ19 ምርጫን ማራዘም እና “ የህግ አማራጮች” በሚል ርዕስ ውይይት ተካሄደ::በኮቪድ19 ምክንያት ቀጣዩን ምርጫ ለማካሄድ አስቸጋሪ በመሆኑ መንግስት አራት የመፍትሄ አማራጮችን አቅርቧል።“ኮቪድ19 ምርጫን ማራዘም እና የህግ አማራጮች” በሚል ርዕስ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት መንግስት ከተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር  ነዉ ውይይት ያካሄደዉ፡፡ ኢትዮጵያ በህገ መንግስቱ መሰረት እስከ ነሃሴ […]

የቱርክ መንግስት ለኮቪድ -19 ወረርሽኝ መከላከል ተግባር የሚውሉ ቁሳቁሶችን ድጋፍ አደረገ::

አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 21 ፣ 2012 የቱርክ መንግስት ለኮቪድ -19 ወረርሽኝ መከላከል ተግባር የሚውሉ ቁሳቁሶችን ድጋፍ አደረገ:: የቱርክ መንግስት ለኮቪድ -19 ወረርሽኝ መከላከል ተግባር የሚውሉ  ድጋፍ ያደረጉ የተለያዩ ቁሳቁሶችን ለኢ.ፌ.ዴ.ሪ የሴቶች፣ ሕጻናትና ወጣቶች ሚኒስቴር አስረክቧል፡፡ድጋፉ በዋነኝነት ለኮቪድ 19 በሽታ መከላከያ ተግባር የሚውሉ ሲሆን 280 ካርቶን ወይም 1 ሺህ 700 ኪሎ ግራም የሆነ የንጽሕና መጠበቂያ ቁሳቁሶች፣ […]

ሞሮኮ በማረሚያ ቤቶቿ ባደረገችው ምርመራ ከ300 በላይ ታራሚዎች በኮቪድ 19 መያዛቸውን አረጋገጠች::

አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 21 ፣ 2012 ሞሮኮ በማረሚያ ቤቶቿ ባደረገችው ምርመራ ከ300 በላይ ታራሚዎች በኮቪድ 19 መያዛቸውን አረጋገጠች:: ይሄ ቁጥር የተገኘው በሶስት እስር ቤቶች በሚገኙ 1 ሺህ 736 እስረኞች ላይ በተደረገ ምርመራ መሆኑን አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ በዘገባው አስነብቧል፡፡ከነዚህ ሶስት እስር ቤቶች መካከል ደግሞ 303 በኮሮና ቫይረስ የተያዙት ሰዎች የተገኙት በሀገሪቱ ደቡባዊ ክፍል በሚገኝ ኦዋራዛቴ […]

በማሊ የሥደተኞች ጣቢያ በእሳት በመውደሙ ዜጎች ለሁለተኛ ስደት ተጋልጠዋል::

አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 21 ፣ 2012 በማሊ የሥደተኞች ጣቢያ በእሳት በመውደሙ ዜጎች ለሁለተኛ ስደት ተጋልጠዋል:: በማሊ በተከሰተው የርስበበርስ ግጭት ምክንያት መኖሪያ ቀያቸውን ለቀው በጊዜያዊ መጠለያ የነበሩ ሰዎች መኖሪያቸው ሙሉ በሙሉ መውደሙ ተሰምቷል፡፡አሶሼትድ ፕሬስ እንደዘገበው በዚህ ጊዜያዊ መጠለያ ጣቢያ ውስጥ እስከ ሁለት ዓመት የቆዩ ከ1 ሺህ በላይ የሚሆኑ ማሊያዊያን ስደተኞች ይኖሩ ነበር፡፡ ስደተኞቹ እንደተናገሩት አለን […]

ምክር ቤቱ ምርጫ ቦርድ ጠቅላላ ምርጫን በተመለከተ ያቀረበውን የውሳኔ ሀሳብ ለዝርዝር እይታ ለቋሚ ኮሚቴ መራ::

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 22፣ 2012 ምክር ቤቱ ምርጫ ቦርድ ጠቅላላ ምርጫን በተመለከተ ያቀረበውን የውሳኔ ሀሳብ ለዝርዝር እይታ ለቋሚ ኮሚቴ መራ የኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የመሰብሰቢያ አደራሽ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባውም የተለያዩ ውሳኔዎችን መርምሮ አጽድቋል።ምክር ቤቱ በመደበኛ ስብሰባው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጠቅላላ ምርጫን በተመለከተ ያቀረበውን የውሳኔ ሐሳብን ተመልክቷል።የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ […]

ኢትዮጵያ ተ.መ.ድ ኮቪድ-19ን ለመግታት የጀመረውን ኢኒሺየቲቭ እንደምትደግፍ  ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ገለጹ::

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 22፣ 2012 ኢትዮጵያ ተ.መ.ድ ኮቪድ-19ን ለመግታት የጀመረውን ኢኒሺየቲቭ እንደምትደግፍ  ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ገለጹ:: የተባበሩት መንግስታት ባለአደራ ፈንድ ለኮቪድ 19 ምላሽ ለመስጠት የጀመረውን “Rise for All” ኢኒሺየቲቭ ኢትዮጵያ መቀላቀሏን ፕሬዚዳንቷ ትናንት አስታውቀዋል።በተመድ ምክትል ዋና ጸሃፊ አሚና መሃመድ ይፋ የሆነው ፕሮጀክት የዓለም ሴት መሪዎች ወረርሽኙ ያስከተለውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳት ለመግታት የሚረዳ መፍትሄ ለማበጀት ህብረታቸውን፣ ጥረታቸውንና ሃብታቸውን በማቀናጀትና በማንቀሳቀስ እንዲሰሩ ጥሪ አቅርቧል።ከፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ በተጨማሪ የኖርዌይ ጠቅላይ ሚኒስትር ኢርና ሶልበርግና የባርባዶስ አቻቸው ሚያ ሞትሊ የተ.መ.ድ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተሮች ፕሮጀክቱን ለመደገፍ  የሚያግዝ የቪዲዮ ውይይት አድርገዋል። “ኮቪድ19 ዓለም አቀፍ ቀውስ መሆኑን ተከትሎ ምላሽ ለመስጠት መዘግየት ሞትን መጥት ነው፤ ሁላችንም ተመሳሳይ ጠላትን የተጋፈጥን በመሆናችን ሰብዓዊ አቅማችንን አንድ ላይ በማስተባበር ለውጤት መሰለፍ አለብን” ብለዋል ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ። “ቫይረሱን በተናጠል ወይም በአንድ አገር ጥረት ብቻ መግታት ስለማይቻል ተመድ ጋራ ትብብር ያቀረበውን ጥሪ እደግፋለሁ” ብለዋል።  የፈንዱ ግብ በመጀመሪያዎቹ ዘጠኝ ወራት 1 ቢሊዮን ዶላር ማሰባሰብ ሲሆን በሁለት አመታት ውስጥ ደግሞ ሁለት ቢሊዮን ዶላር ለማሰባሰብ ያለመ ነው።በዚህም ዝቅተኛና መካከለኛ ገቢ ያላቸውን አገሮች፣ ህፃናትን፣ ሴቶችንና ለአደጋ የተጋለጡ  የማህበረሰብ ክፍሎችን ለመደገፍ አቅጣጫ ተይዟል።

ሚኒስቴሩ በሃብት ማሰባሰብ ስትራቴጂ ካሰባሰበዉ ሀብት ዉስጥ 15 ሚሊዮን ብሩን ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸዉ ተቋማት አስረከበ፡፡

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 22፣ 2012 ሚኒስቴሩ በሃብት ማሰባሰብ ስትራቴጂ ካሰባሰበዉ ሀብት ዉስጥ 15 ሚሊዮን ብሩን ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸዉ ተቋማት አስረከበ፡፡የሴቶች፣ ህፃናትና ወጣቶች ሚኒስቴር ለአርትስ በላከዉ መግለጫ እንዳስታወቀዉ፤ ሚኒስቴሩ ባካሄደዉ የርክክብ ስነስርዓት ላይ የተገኙት የወጣቶች ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ ወ/ሮ ህይወት ኃይሉ ባስተላለፉት መልዕክት ቫይረሱ በፍጥነት የሚዛመት በመሆኑ የቆየንበት  የመጠጋጋት፣ የመጨባበጥና የመሳሳም ልማድን መተዉ አለብን ብለዋል፡፡ ሚኒስትር ዲኤታዋ […]