loading
አይቤክስ ኮሌጅ ከፍለው መማር ለማይችሉ 150 ዜጎች ነፃ የትምህርት ዕድል ተጠቃሚ ማድረጉን አስታወቀ፡፡

አዲስ አበባ፣ጥር 24፣ 2013 አይቤክስ ኮሌጅ ከፍለው መማር ለማይችሉ 150 ዜጎች ነፃ የትምህርት ዕድል ተጠቃሚ ማድረጉን አስታወቀ፡፡ ኮሌጁ ከተቋቋመ ከ2002 ጀምሮ በሆቴል እና ቱሪዝም ዘርፍ ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር መጀመሩን ያስታወሱት የኮሌጁ ዲን አቶ ተስፍዬ አሰፋ ፤ እስካሁን ድረስ ከፍለው መማር ለማይችሉ 150 ዜጎች ነፃ የትምህርት ዕድል በመስጠት ወደ ስራ ማስግባታቸውን ተናግረዋል። በዘንድሮው ዓመት በሆቴል ማኔጅመንት […]

ሞቃዲሾ ውስጥ የደረሰ የቦንብ አደጋ የሞትና የአካል ጉዳት አድርሷል ተባለ::

አዲስ አበባ፣ጥር 24፣ 2013 ሞቃዲሾ ውስጥ የደረሰ የቦንብ አደጋ የሞትና የአካል ጉዳት አድርሷል ተባለ:: አደጋው የተፈፀመው በማዕከላዊ ሞቃዲሾ በሚገኘው አፍሪክ ሆቴል ላይ ሲሆን ታጣቂዎች በአካባቢው ሁከት ከፈጠሩ በኋላ ፍንዳታው መከተሉን የዓይን እማኞች ተናግረዋል፡፡ በአደጋው ሳቢያ አንድ ጡረተኛ የጦር ጄኔራልን ጨምሮ አምስት ሰዎች ህይዎታቸው ማለፉ ተሰምቷል፡፡ ከሟቾቹ በተጨማሪ 10 ሰዎች በአደጋው ምክንያት የመቁሰል አደጋ እንደደረሰባቸው አፍሪካ […]

ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ሁለት አዳዲስ የህግ ጠበቆችን መቅጠራቸው ተሰማ::

አዲስ አበባ፣ጥር 24፣ 2013 ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ሁለት አዳዲስ የህግ ጠበቆችን መቅጠራቸው ተሰማ:: የቀድሞው ፕሬዚዳንት በስልጣን ላይ በነበሩበት ወቅት ህግ ተላልፈዋል መባላቸውን ተከትሎ ክስ ስለሚጠብቃቸው ራሳቸውን ለመከላkል ነው ይህን ያደረጉት ተብሏል፡፡ ትራምፕ ከሚጠብቃቸው ክስ ይከላከሉልኛል ያሏቸውን ዴቪድ ሾን እና ብሩስ ካስቶር የተባሉ የህግ ጠበቆችን መቅጠራቸውን ይፋ አድርገዋል፡፡ ትራምፕ አዳዲስ ጠበቆችን ለመቅጠር የተገደዱት የቀድሞዎቹ ጠበቆቻቸው ከሳቸው […]

ተጋነነ ዋጋ በሚያስከፍሉ ጫኝና አውራጆች ላይ ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድ ተገለፀ፡፡

አዲስ አበባ፣ጥር 27፣ 2013 ተጋነነ ዋጋ በሚያስከፍሉ ጫኝና አውራጆች ላይ ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድ ተገለፀ፡፡ ዕቃ ለማውረድና ለመጫን የተጋነነ ዋጋን የሚጠይቁ ጫኝና አውራጆችን የማጣራት ሥራ በማድረግ ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሸን አስታወቀ። የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ኮማንደር ፋሲካ ፋንታ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንዳስታወቁት፣ ለዕቃ ማውረድና መጫን የሚከፈለው ገንዘብ በዕቃ ባለቤትና በአውራጁ መካከል በሚደረገው […]

የአማዞን ቀጣይ ስራ አስፈጻሚ ይሆናል የተባለው ኤንዲ ጄሲ ማነው?

አዲስ አበባ፣ጥር 27፣ 2013 የአማዞን ቀጣይ ስራ አስፈጻሚ ይሆናል የተባለው ኤንዲ ጄሲ ማነው? ከዓለማችን ቁንጮ ቱጃሮች መካከል 2ኛው የሆነው ቤዞስ በግዙፉ የዓለማችን የበይነ መረብ ግብይት ተቋም አማዞን ያለውን ኃላፊነት ለሌላ ሰው እንደሚያስረክብ አስታውቋል፡፡ ቤዞስ የአማዞን መስራች እና ዋና ስራ አስፈጻሚ ነው፡፡ ትኩረቱን ወደ ሌሎች የቢዝነስ ዘርፎች የማዞር ውጥን እንዳለው ያስታወቀው ቤዞስ ዋና ስራ አስፈጻሚነቱን በመጪው […]

የተፈናቀሉ ዜጎች በምርጫው የሚሳተፉበት አሰራር መዘጋጀቱን ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ ገለጹ፡፡

አዲስ አበባ፣ጥር 28፣ 2013 የተፈናቀሉ ዜጎች በምርጫው የሚሳተፉበት አሰራር መዘጋጀቱን ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ ገለጹ፡፡ የተፈናቀሉ ዜጎች በ6ኛው አገራዊ ምርጫ የሚሳተፉበት አሰራር መዘጋጀቱን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ ገለጸዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ ”ይጠይቁ” በሚል ርዕስ በተዘጋጀው የማህበራዊ ሚዲያ የተሳትፎ መድረክ ለቀረቡ ጥያቄዎች በቦርዱ የፌስቡክ ገጽ በቀጥታ ምላሽ ሰጥተዋል። […]

በየመን የአልቃይዳ መሪ ካሊድ ባታርፊ በቁጥጥር ስር ውሏል ተባለ::

አዲስ አበባ፣ጥር 28፣ 2013 በየመን የአልቃይዳ መሪ ካሊድ ባታርፊ በቁጥጥር ስር ውሏል ተባለ:: የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በየመን የአልቃይዳ መሪ በቁጥጥር ስር መዋሉን አስታወቀ፡፡ የመንግስታቱ ድርጅት የክትትል ቡድን ትናንት ሃሙስ ለጸጥታው ምክር ቤት ባቀረበው ሪፖርት ካሊድ ባታርፊ በቁጥጥር ስር ከዋለ መቆየቱን ጠቁሟል፡፡ በየመን የአልቃይዳ መሪዉ ባታርፊ በፈረንጆቹ 2020 መጀመሪያ አመታ ላይ  ነበር የሽብር ቡድኑን እንዲመራ የተመረጠው እንደ […]

ቻይና ለ50 ዓመታት የዘለቀውን አጋርነቷን አጠናክራ እንደምትቀጥል ገለጸች::

አዲስ አበባ፣ጥር 28፣ 2013 ቻይና ለ50 ዓመታት የዘለቀውን አጋርነቷን አጠናክራ እንደምትቀጥል ገለጸች:: የኢፌድሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ዣኦ ዢዩአንን ተቀብለው ያነጋገሩ ሲሆኑ : በሁለቱ አገሮች መካከል ስላለው የተጠናከረ ግንኙነትና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል። አምባሳደር ዣኦ ዢዩአን ኢትዮጵያና ቻይና 50 አመታትን የዘለቀ በመተባባር ላይ የተመሰረተ ጠንካራ ወዳጅነት እንዳላቸው አንስተዋል፡፡ […]

የኮቪድ 19 ክትባት ተስፋና ስጋት በኢትዮጵያ በሚል ርእሰ ውይይት ተካሄደ።

አዲስ አበባ፣ጥር 30፣ 2013  የኮቪድ 19 ክትባት ተስፋና ስጋት በኢትዮጵያ በሚል ርእሰ ውይይት ተካሄደ። በዶክተር እናውጋው መሀሪ መስራችነት የተቋቋመው ፒፕል ቱ ፒፕል በጎ አድራጎት ድርጅት እና የኢትዮጵያ ዲያስፖራ አድቮኬሲ ካውንስል ኦን ኮቪድ 19 አማካኝነት በዌቢናር ነው ውይይቱ የተካሄደው ። በውይይቱ የኮቪድ 19 ክትባት ተስፋና ስጋት በኢትዮጵያ ምን ይመስላል ፧የሚለው ጉዳይ ላይ ጥናታዊ ጽሁፍ ቀርቧል። የዲያስፖራው […]

ሚኒስቴሩ የኮቪድ -19 በሽታን ከመከላከል አንጻር ባለፉት 6 ወራት ዉጤታማ ስራዎችን ሰርቼያለሁ አለ፡፡

አዲስ አበባ፣የካቲት 3፣ 2013 ሚኒስቴሩ የኮቪድ -19 በሽታን ከመከላከል አንጻር ባለፉት 6 ወራት ዉጤታማ ስራዎችን ሰርቼያለሁ አለ፡፡ የሴቶች፣ ሕፃናትና ወጣቶች ሚኒስቴር ለአርትስ በላከዉ መግለጫ በ2013 በጀት አመት ባለፉት 6 ወራት የኮቪድ ወረርሺኝ ለመከላከል እንዲያግዝ በመላ ሀገሪቱ ከ74 ሚሊዮን ብር በላይ ሀብት ማሰባሰብ መቻሉን ገልጿል፡፡ በተጨማሪም በአማራ ክልል በአይነት እህል 1በንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁሶች እና በቤት ዉስጥ […]