loading
ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ዘውዴ በጦር ግንባር ጀብድ ፈፅመው ድል ላመጡ ሴቶች ምስጋና አቀረቡ::

አዲስ አበባ፣ የካቲት 29፣ 2014 ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን በተለያዩ ዝግጅቶች በመከላከያ መኮንኖች ክበብ ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ዘውዴ በተገኙበት ተከብሯል። ፕሬዚዳንቷ በዚህ ወቅት ሴት የመከላከያ ሰራዊት አባላት በናንተ ድርብ መስዋዕትነት ሀገር ትቀጥላለችና ለናንተ ክብር መስጠት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ የሀገራችን ሰላም በሴቶች ተጋድሎ ይረጋገጣል፤ በጀግና ሴቶች ሰማዕትነት ሀገራችን ታፍራ እና ተከብራ ትኖራለችም ብለዋል፡፡ አሸባሪው የህወሓት ቡድን በኢትዮጵያ ላይ […]

በሴት የሕክምና ባለሙያዎች ብቻ የተመራ የቀዶ ሕክምና የቅዱስ ጳውሎስ ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ::

አዲስ አበባ፣ የካቲት 29፣ 2014 በሴት የሕክምና ባለሙያዎች ብቻ የተመራ የቀዶ ሕክምና የቅዱስ ጳውሎስ ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ:: ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን አስመልክቶ በሴት የሕክምና ባለሙያዎች ብቻ የተመራ የቀዶ ሕክምና አገልግሎት ሰጠ፡፡ ሆስፒታሉ በሴት ሐኪሞች ብቻ በሚመራው በዚህ መርሀ ግብሩ ለ23 ያህል ሕሙማን ቀዶ ሕክምና እሰጣለሁ ብሏል፡፡ የሴቶች ሕክምና ቡድኑን የሚመሩት ዶ/ር መሰረት ሕይወቴ የቀዶ ሕክምና […]

ሱዳን በቀይ ባህር አካባቢ ሩሲያ የጦር ሰፈር እንድታቋቁም መፍቀዷ ግብፅን ቅር አሰኝቷል ተባለ፡፡

አዲስ አበባ፣ የካቲት 29፣ 2014 ሱዳን በቀይ ባህር አካባቢ ሩሲያ የጦር ሰፈር እንድታቋቁም መፍቀዷ ግብፅን ቅር አሰኝቷል ተባለ፡፡ የሱዳንን ሉዓላዊ ምክር ቤትን በምክትልነት የሚመሩት ጄኔራል ሞሃመድ ሃምዳን ዳጋሎ ሞስኮ ደርሰው በተመለሱ ማግስት ሀገራቸው ለሩሲያ የጦር ሰፈር ግንባታ መፍቀዷን ይፋ አድርገዋል፡፡ዳጋሎ በመግለጫቸው ይህን በማድረጋችን ብሔራዊ ጥቅማችን እስካልተነካ ድረስ ስህተት የለውም የሚፈጥረው የፀጥታ ስጋትም የለም ብለዋል፡፡ የግብጽ […]