loading
ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ካፒታል ስራውን የሚጀምረው አማራ ባንክ

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 6 ፣ 2014 አማራ ባንክ አክሲዮን ማህበር በሳምንቱ መጨረሻ ሥራውን በይፋ እንደሚጀምር ይፋ አደረገ፡፡ ባንኩ በ6 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር መነሻ ካፒታል ሰኔ 11 ቀን 2014 ዓ.ም ስራውን በይፋ እንደሚጀምር ነው ያስታወቀው፡፡ የባንኩን ስራ የመጀመር ሂደትን አስመልክቶ የባንኩ ከፍተኛ አመራሮች መግለጫ ጋዜጣዊ ሰጥተዋል። በ6 ቢሊዮን 516 ሚሊዮን ብር በላይ በተከፈለ የመነሻ […]

ሞስኮን ያልበረገራት የምእራባዊያን የነዳጅ ማእቀብ

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 6 ፣ 2014 በሩሲያ ላይ የተጣለው የነዳጅ ግብይት ማእቀብ ግቡን እዳልመታ የሚገልጽ አዲስ ሪፖርት ይፋ ሆነ፡፡ ሪፖርቱ ፕሬዚዳንት ቭላደሚር ፑቲን ጦራቸውን ወደ ዩክሬን ባዘመቱ በ100 ቀናት ውስጥ ሞስኮ ከነዳጅ ሽያጭ 98 ቢሊዮን ዶላር ማግኘቷን ይገልጻል፡፡ ይህን ሪፖርት ይፋ ያደረገው ተቀማጭነቱ ፊንላንድ የሆነ በኢነርጂና ንጹህ አየር ላይ ምርምር የሚያደርግ ገለልተኛ ተቋም ነው […]

የትምህርትን የጥራት ችግር ለመፍታት በልዩ ትኩረት ይሰራል-ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2014 በትምህርት ስርአቱ ላይ የሚስተዋለውን የጥራት ችግር ለመፍታት የተጀመሩ የሪፎርም ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ገለጹ። ሚኒስትሩ ይህን ያሉት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች አዲስ ከተመደቡት የከፍተኛ ትምህርት የቦርድ አመራሮች ጋር ውይይት ባደረጉበት ወቅት ነው፡፡ፕሮፌሰር ብርሃኑ በዘርፉ የአምስት አመት ዋነኛ የትኩረት አቅጣጫዎች መካከል የከፍተኛ ትምህርት አግባብነት እና ጥራት ማረጋገጥ በመሆኑ […]

ትራምፕ እንዲከሰሱ ድምፅ የሰጡት ተወካይ በምርጫ መሸነፍ…

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2014 በካፒቶል ህንፃ በተነሳው ግርግር ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እንዲከሰሱ ድምፅ የሰጡት የሪፓበሊካን ተወካይ በዳግም ምርጫ ተሸነፉ፡፡ በኖርዝ ካሮላይና ለአምስት ዓመታት በህግ አውጭ ምክር ቤት ተወካይነት ያገለገሉት ቶም ራይስ የተሸነፉት በቀድሞው ፕሬዚዳንት በሚደገፉት ሩሴል ፍራይ በተባሉ እጩ መሆኑን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡ ፍራይ ማሸነፋቸውን ካወቁ በኋላ ባደረጉት ንግግር መራጩ ህዝብ በግልፅ ቋንቋ በካርዱ ተናግሯል፤ […]

ጥቃት አድራሾችን ከእንግዲህ አንታገሳቸውም-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 13፣ 2014 ጥቃት በደረሰባቸው አካባቢዎች ሰላም እና ደህንነትን መመለስ ቅድሚያ የሚሰጠው ተግባር መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ተናገሩ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባስተላለፉት መልእክት “በንጹሃን ዜጎች ላይ በህገወጥ እና በኢ-መደበኛ ኃይሎች የሚደርስ ጥቃት እና የዜጎችን መተዳደሪያ ማውደም ተቀባይነት የለውም” ብለዋል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በቤኒንሻንጉል እና ኦሮሚያ ክልሎች፣ ዋና ዓላማቸው ኅብረተሰቡን ማሸበር […]

በአዲስ አበባ የ3ኛ ዙር የኮቪድ 19 መከላከያ ክትባት ዘመቻ በዛሬው ዕለት መሰጠት ተጀመረ፡፡

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 13፣ 2014 ለቀጣዮቹ 10 ተከታታይ ቀናት በሚሰጠው ክትባት ዕድሜያቸው12 ዓመትና ከዚያ በላይ የሆናቸው ሁሉ አገልሎቱን እንደሚያገኙ ተገልጿል፡፡ ክትባቱ በሁሉም የመንግስት ጤና ጣቢያዎችና ሌሎች የተመረጡ ጊዜያዊ የክትባት መስጫ ጣቢያዎች በዘመቻ መልክ እንደሚሰጥ ታውቋል፡፡ በዚህ የ3ኛው ዙር የክትባት ዘመቻም መጠኑ 249 ሺህ የሚሆን የክትባት ዶዝ ለመስጠት መታቀዱን ከአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡ […]

የተወካዮች ምክር ቤት አሸባሪው የሸኔ ቡድን በምዕራብ ወለጋ በንጹሀን ዜጎች ላይ ያደረሰውን አደጋ በፅኑ አወገዘ፡

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 28፣ 2014 የተወካዮች ምክር ቤት አሸባሪው የሸኔ ቡድን በምዕራብ ወለጋ በንጹሀን ዜጎች ላይ ያደረሰውን አደጋ በፅኑ አወገዘ፡፡ ምክር ቤቱ የሽብር ቡድኑ በጸጥታ ሀይሎች ጥቃት እየደረሰበት በመሆኑ ከጥቃቱ በመሸሽ በምዕራብ ወለጋ ንጹሀን ዜጎች ላይ አደጋ አድርሷል ብሏል። በኦሮሚያ ክልል፣ ቄለም ወለጋ ዞን የሚገኙ ንጹሀን ዜጎቻችን ላይ የፈጸመው ጭፍጨፋ በእጅጉ የሚወገዝ መሆኑን አስታውቋል፡፡ በዜጎቻችን […]

የመንግስት ህግ የማስከበር ሀላፊነት ጥያቄ ውስጥ መግባቱ አሳስቦኛል -ኢዜማ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 28፣ 2014 የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ ኢዜማ ፓርቲ መንግስት የህግ የበላይነትን የማስከበር ሃላፊነቱ ከዕለት ዕለት ጥያቄ ውስጥ እየገባ መምጣቱ በብርቱ አስግቶኛል አለ።ፓርቲው ይህን ያለው በቄለም ወለጋ በንጹሀን ዜጎች ላይ የደረሰውን አሰቃቂ ግድያ አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ ነው፡፡ ኢዜማ “በድንገት መጥቶ ህዝብን ከሚያጠቃው እኩይ አካል እኩል ዜጋውን የመጠበቅ ግዴታ ኖሮበት የማይጠብቀው መንግስት ተጠያቂ ነው” […]

የሱዳኑ ሉዓላዊ ምክር ቤት መሪ ጄኔራል አብዱል ፈታህ አልቡርሃን ጦር ሰራዊቱ ከመንግስት አስተዳዳሪነቱ እንደሚነሳ አስታወቁ፡፡

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 28፣ 2014 የሱዳኑ ሉዓላዊ ምክር ቤት መሪ ጄኔራል አብዱል ፈታህ አልቡርሃን ጦር ሰራዊቱ ከመንግስት አስተዳዳሪነቱ እንደሚነሳ አስታወቁ፡፡በመፈንቅለ መንግስት የመሪነቱን ስፍራ የያዙት አል ቡርሃን ጦሩ ከፖለቲካዊ ውይይቶች ራሱን እንደሚያግል ያስታወቁ ሲሆን የሲቪል የሽግግር መንግስት እንዲመሰርቱ እንደሚፈቅድ ገልፀዋል። የጄኔራሉ መግለጫ የተሰማው ካለፈው ሳምንት ጀምሮ ወታደራዊ አገዛዝ እንዲያበቃ የሚጠይቁ መጠነ ሰፊ ህዝባዊ ተቃውሞዎች መቀጠላቸውን ተከትሎ […]

በቀን ኮታ የተደለደለው የነዳጅ ስርጭት

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 29 ፣ 2014 የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ተሽከርካሪዎች በቀን መሙላት የሚችሉት የነዳጅ ኮታ ድልድል ይፋ ሆነ፡፡ የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ተሽከርካሪዎችን ብቻ ተጠቃሚ የሚያደርገው አዲሱ የነዳጅ ድጎማ ከዛሬ ጀምሮ ተግባራዊ መሆን ጀምሯል፡፡ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪ ተሽከርካሪዎች የታለመለት የነዳጅ ድጎማ ተጠቃሚ ለመሆን አስፈላጊ መረጃዎችን በመስጠት በኢትዮ ቴሌኮም የሽያጭ […]