loading
በናይጀሪያ የቦኩሀራም ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት 81 ሰዎች ተገደሉ::

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2012  በናይጀሪያ የቦኩሀራም ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት 81 ሰዎች ተገደሉ:: ታጣቂዎቹ ሞንጉኖ እና ንጋንዛይ በተባሉት የሀገሪቱ አካባቢዎች ላውንቸር እና ሮኬቶችን ጭምር ታጥቀው ከባድ ጥቃት ማድረሳቸውን የአካባው ነዋሪዎች እና የእርዳታ ሰራተኞች ተናግረዋል፡፡ በጥቃቱ 20 የሚሆኑ የመንግስት ወታደሮች የተገደሉ ሲሆን በስፍራው የነበሩ ቀሪዎቹ ወታሮችም ተዋጊዎችን መመከት አቅቷቸው ሲሸሹ ታይተዋል ነው የተባለው፡፡ የመንግስት ወታደሮችን ጨምሮ […]

የቱርክ ተዋጊ ጄቶች በሰሜናዊ ኢራቅ በሚገኘው የፒኬኬ የጦር ሰፈር ድብደባ ፈጸሙ፡፡

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2012  የቱርክ ተዋጊ ጄቶች በሰሜናዊ ኢራቅ በሚገኘው የፒኬኬ የጦር ሰፈር ድብደባ ፈጸሙ፡፡የጦር ጄቶቹ ከቱርክ የተለያዩ የአየር ሃይል ማረፊያዎች በመነሳት የፒኬኬ ዋነኛ የጦር ካምፕን ጨምሮ በሰሜናዊ ኢራቅ የሚገኙ በርካታ ስፍራዎች ላይ ጥቃት አድርሰዋል፡፡እንደ ሀገሪቱ መከላከያ ሚኒስቴር ከሆነ የጦር ድብደባው በቱርክ የጦር ካምፕ ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶች እየጨመሩ በመምጣታቸው የተወሰደ የአፀፋ እርምጃ ነው፡፡የቱርክ መከላከያ […]

ከ90 ዓመታት በኃላ በህብረተሰቡ ተሳትፎ ሙሉ እድሳት የተደረገለት የነቀምቴ እስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የተሻለ አገልግሎት መስጠት ጀመረ ::

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 8 ፣ 2012 ከ90 ዓመታት በኃላ በህብረተሰቡ ተሳትፎ ሙሉ እድሳት የተደረገለት የነቀምቴ እስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የተሻለ አገልግሎት መስጠት ጀመረ ::የምስራቅ ወለጋ ዞን የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ለአርትስ በላከዉ መግለጫ የነቀምቴ እስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለበርካታ ዓመታት እድሳት ሳይደረግለት የቆየና ለአመታት በብልሹ አሰራርና ለታካሚዎች አመቺ ባለመሆኑ ከህብረተሰቡ በርካታ ቅሬታዎችና ወቀሳዎችን ሲያስተናግድ እንደቆየ ገልጿል፡፡ሆስፒታሉ እድሳት የተደረገለት […]

ፖፕ ፍራንሲስ በሊቢያ የሚካሄደው ውጊያ እንዲቆም ጥሪ አቀረቡ፡፡

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 8 ፣ 2012 ፖፕ ፍራንሲስ በሊቢያ የሚካሄደው ውጊያ እንዲቆም ጥሪ አቀረቡ፡፡ የሮማው ሊቀጳጳስ ፍራንሲስ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ባስተላለፉት መልዕክት እባካችሁ ይህች ሀገር ከብጥብጥ ወጥታ ወደ ሰላም ትመጣ ዘንድ አግዟት ብለዋል፡፡ አፍሪካ ኒውስ እንደዘገበው ሊቀጳጳስ ፍራንሲስ በቅዱስ ጴጥሮች አደባባይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር በሀገሪቱ እየተደረገ ባለው የእርስ በርስ ጦርነት ከልባቸው ማዘናቸውን ተናግረዋል፡፡ በሊቢያ […]

በኢትዮጵያ ተጨማሪ 176 ሰዎች የኮሮናቫይረስ ሲገኝባቸዉ 75 ሰዎች ደግሞ ማገገማቸዉ ተገለጸ፡፡

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 8 ፣ 2012 በኢትዮጵያ ተጨማሪ 176 ሰዎች የኮሮናቫይረስ ሲገኝባቸዉ 75 ሰዎች ደግሞ ማገገማቸዉ ተገለጸ፡፡ባለፉት 24 ሰዓታት በተደረገ ዉ 5 ሺ 6 መቶ 36 የላብራቶሪ ምርመራ አንድመቶ ሰባስድስት ሰዎች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸዉ የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ አስታዉቀዋል፡፡በአጠቃላይም በሀገራችን ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸዉ ሰዎች ቁጥር 3 ሺህ 5 መቶ 21 ደርሷል፡፡ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸዉ ሰዎች […]

ከ1ነጥብ 3 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ የላብራቶሪ መሳሪያዎች ድጋፍ ተደረገ::

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 8 ፣ 2012  ከ1ነጥብ 3 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ የላብራቶሪ መሳሪያዎች ድጋፍ ተደረገ:: የጤና ሚኒስቴር እንዳስታወቀዉ ሬይ አስመጪ እና ላኪ ኃ/ተ/ግ/ድርጅት በዛሬ ዕለት ለኮሮና መከላከያ የሚውሉ የላብራቶሪ መመርመሪያ መሳሪያዎች ለ ሚኒስቴሩ አስረክበዋል ፡፡ በርክክቡም ወቅት የጤና ሚኒስቴር ተወካይ አቶ ያዕቆብ ሰማን እንደተናገሩት የተደረገው ድጋፍ ለኮሮና በሽታ ለይቶ ህክምና መስጫ ማዕከሎች አገልግሎት […]

በዲሞክራቲክ ሪፓብሊክ ኮንጎ የተከሰተው የኢቦላ ቫይረስ 11 ሰዎችን መግደሉ ተሰማ::

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 9 ፣2012  በዲሞክራቲክ ሪፓብሊክ ኮንጎ የተከሰተው የኢቦላ ቫይረስ 11 ሰዎችን መግደሉ ተሰማ:: ምእራብ አፍሪካዊቷ ሪፓብሊክ ኮንጎ በአሁኑ ጊዜ ሶስት ትላልቅ ፈተናዎች ከፊቷ ተጋርጠውባታል ነው የተባለው፡፡ አንደኛው የመላው ዓለም ችግር የሆነው የኮሮና ቫይረስ፣ ሁለተኛው ደጋግሞ ያንገላታት የኢቦላ ቫይረስ ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ ከኩፍኝ ወረርሽኝ ጋርም እየታገለች ነው፡፡ አልጀዚራ እንደዘገበው በዲሞክራቲክ ኮንጎ በቅርቡ […]

የአፍሪካ ህጻናት ቀን የኢኮኖሚ ጫና ለገጠማቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ በማድረግ እየተከበረ ነው::

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2012 የአፍሪካ ህጻናት ቀን የኢኮኖሚ ጫና ለገጠማቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ በማድረግ እየተከበረ ነው:: የአፍሪካ ህጻናት ቀን በኮቪድ-19 ምክንያት የኢኮኖሚ ጫና ለገጠማቸው ዝቅተኛ የህብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ በማድረግና ግንዛቤ በመስጠት እየተከበረ መሆኑን የሴቶች፣ ህጻናትና ወጣቶች ሚኒስቴር አስታወቀ :: ሚኒስቴሩ ለአርትስ በላከዉ መግለጫ እንዳስታወቀዉ የአፍሪካ ህጻናት ቀንን ከሰኔ 2 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ በዓሉን […]

በኒው ዚላንድ ከ24 ቀናት በኋላ ሁለት የኮሮሮናቫይረስ ታማሚዎች መገኘታቸው ተሰማ::

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2012 በኒው ዚላንድ ከ24 ቀናት በኋላ ሁለት የኮሮሮናቫይረስ ታማሚዎች መገኘታቸው ተሰማ:: ቢቢሲ በዘገባው እንዳስነበበው ኒው ዚላንድ የኮሮናቫይረስን አጥፍቻለሁ ካለች በኋላ ነው ከእንግሊዝ በመጡ ሁለት ሰዎች ቫይረሱ የተገኘው፡፡ ኒው ዚላንድ ባለፈው ሳምንት አዲስ የኮሮናቫይረስ ታማሚዎች አለመገኘታቸውን ተከትሎ በሀገር ውስጥ ጥላቸው የነበሩትን የዕንቅስቃሴ እገዳዎች ሙሉ በሙሉ አንስታለች፡፡ አሁን ላይ ከእንግሊዝ በልዩ ፈቃድ ወደ […]

የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አካል የሆነው የቤት እድሳት መርሀግብር በይፋ ተጀመረ::

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2012 የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አካል የሆነው የቤት እድሳት መርሀግብር በይፋ ተጀመረ::ኢ/ር ታከለ ኡማ በሚኖሩበት አካባቢ ነዋሪ የሆኑት ወ/ሮ ቀነኒ ሁንዴ መኖሪያ ቤት በመገኘት የቤት እድሳት መርሀግብሩን አስጀምረዋል :: በየአካባቢው የሚገኙ ለኑሮ አስቸጋሪ በሆነ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ አቅመደካማች መኖሪያ ቤታቸው የሚታደስ ይሆናል :: በመኖሪያ ቤት እድሳቱ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሰጪ ወጣቶችና […]