loading
የተባበሩት መንገስታት ድርጅት ባለፈው ዓመት ብቻ በዓለም 80 ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች ከመኖሪያቸው ተፈናቅለዋል አለ

የድርጅቱ የስደተኞች ጉዳይ ቢሮ በዓመታዊ ሪፖርቱ ይፋ እንዳደረገው የመፈናቀላቸው መንስኤዎች የርስበርስ ግጭት፣ ጥቃት፣ የሰብዓዊ መብት ጥሰት እና ተያያዥ ችግሮች ናቸው፡፡ አልጀዚራ በዘገባው እንዳስነበበው 79.5 ሚሊዮን ከሚሆኑት ተፈናቃዮች መካከል 26 ሚሊዮን ስደተኞች፣ 4.2 ሚሊዮን ጥገኝነት ጠያቂዎች፣ ከ45 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት ደግሞ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች ናቸው፡፡ በየዓመቱ የሥደተኞች ቁጥር እየጨመረ መሆኑ ያሳሰበው ድርጅቱ በተለይ በየጊዜው የሚከሰቱ ግጭቶች […]

የደቡብ ክልልና አዲሱ የሲዳማ ክልል የስልጣን ርክክብ አካሄዱ

የደቡብ ክልል እና አዲሱ የሲዳማ ክልል በደቡብ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልል ምክር ቤት ፊት ቀርበው የስልጣን ርክክብ አካሄዱ። የደቡብ ብሄሮች ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልል ምክር ቤት 5ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 2ኛ አስቸኳይ ጉባኤ የሲዳማ ዞን በክልል እንዲደራጅ በዛሬው እለት ወስኗል። ምክር ቤቱ እያካሄደ ባለው አስቸኳይ ጉባኤ የሲዳማ ዞን በክልል እንዲደራጅ የወሰነው የሥልጣን ርክብክብ እንዲደረግ […]

የአሜሪካ ማዕከላዊ ባንክ የሥራ አጦች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱ እንዳሳሰበው ገለፀ

ባለፈዉ ሳምንት ብቻአንድ ነጥብ አምስት አሜሪካዊያን የስራ አጥነት ፎርም መሙላታቸው ኮቪድ 19 በሀገሪቱ ጫናውን እንደቀጠለ መሆኑን ያመላክታል ተብሏል፡፡ ቢቢሲ እንደዘገበው በአሜሪካ ለ13 ተከታታይ ሳምንታት የሥራ አጦች ቁጥር ከ1 ሚሊዮን በላይ እየሆነ መመዝገቡ ተስተውሏል፡፡ ይህን ያስተዋለው የሀገሪቱ ማእከላዊ ባንክ አስቸኳይ የኢኮኖሚ ማስተካከያ ካልተደረገ ችግሩ ከዚህም የከፋ ሊሆን እንደሚችል አስጠንቅቋል፡፡ ምንም እንኳ አሜሪካ በኮሮናቫይረስ ምክንያት ተዘግተው የነበሩ […]

የኮቪድ19 ወረርሽኝን ለመግታት የቻይና አፍሪካ ትብብር የማይተካ ሚና አለው አሉ አቶ ገዱ አንዳርጋቸው

የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽ/ቤት ለአርትስ በላከዉ መግለጫ  እንዳስታወቀዉ የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው በዓለም ላይ የተከሰተውን የኮቪድ19 ወረርሽኝ ለመግታት የቻይና አፍሪካ ትብብር የማይተካ ሚና አለዉ ብለዋል የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ትናንት “ዓለም አቀፉ የአንድ ቀበቶ አንድ መንገድ ኢኒሸቲቭ” የቪዲዮ ኮንፈረንስ በተካሄገበት ወቅት እንዳሉት ፤የዓለም ስጋት የሆነውን የኮቪድ19 ወረርሽኝ ለመግታት በቻይና እና አፍሪካ መካከል የሚደረገው ትብብር ከምንጊዜውም በላይ ወሳኝ ነዉ። ቻይና የኮቪድ19 ወረርሽኝን ለመግታት የተከተለችውን ስትራቴጂ እና የተገኘውን ውጤትም አድንቀዋል። ኢትዮጵያ የኮቪድ19 ወረርሽኝን ለመግታት እያደረገች ባለው እንቅስቃሴ የቻይና መንግስት እና እንደ ጃክማ የመሳሰሉ የቻይና በለሃብቶች እያደረጉት ላለው ድጋፍ ያመሰገኑት አቶ ገዱ፥ ድጋፉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ያላቸውን እምነት ገልጸዋል። በኮንፈረንሱ ላይ የቻይና ስቴት ካውንስልና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ይን ጨምሮ የተለያዩ ሃገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች፣ የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ቴዎድሮስ አድሃኖም፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅትና ሌሎች ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ተወካዮች ተሳትፈዋል። “የአንድ ቀበቶ አንድ መንገድ ኢኒሸቲቭ” ዓለም አቀፍ ትብብርን በማሳደግ የኮቪድ19 ወረርሽኝን ለመግታት የሚያስገኘውን ጠቀሜታ በተመለከተ በስፋት መብራራቱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ፅህፈት ቤት የላከልን መግለጫ  ያመለክታል።

ኬንያ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ተለዋጭ አባልነት ምርጫን አሸነፈች

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 12 ፣ 2012  ቢቢሲ እንደዘገበው ከአፍሪካ ሀገራት ኬንያ እና ጂቡቲ በተወዳሩበት ምርጫ ኬንያ ጂቡቲን 129 ለ62 በሆነ የድምፅ ልዩነት በማሸነፍ ነው የምክር ቤቱን መቀመጫ ያገኘችው፡፡የኬንያው ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ጂቡቲን በብርቱ ተፎካካሪነቷ አድንቀው የአፍሪካ ህብረትን ደግሞ ለሀገራቸው ለሰጠው እውቅና አመስግነዋል፡፡ኬንያ ይህን ውድድር ማሸነፏ በአካባቢው ያላት ተሰሚነት ከፍ እያለ የመምጣቱን የሚያመላክት ነው ያሉት […]

በኢትዮጵያ የህክምና ባለሙያዎች በሚያዙት መሰረት ዴክሳሜታዞን ለኮቪድ 19 ህሙማን እንደ ድንገተኛ ህክምና ለመጠቀም ተወሰነ ።

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 12 ፣ 2012  በኢትዮጵያ የህክምና ባለሙያዎች በሚያዙት መሰረት ዴክሳሜታዞን ለኮቪድ 19 ህሙማን እንደ ድንገተኛ ህክምና ለመጠቀም ተወሰነ ።የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ እንዳስታወቁት ;ለኮቪድ-19 ህሙማን የሚውለውን ዴክሳሜታዞን የተባለውን መድሀኒት በተመለከተ በእንግሊዝ መንግስት የተካሄደውን ጥናት እና ሪፖርት በዝርዝር ተመልክተነዋል ብለዋል፡፡የህክምና ጉዳዮች አማካሪ ቡድናችን እና የጤና ባለሙያዎች አማካሪ ምክር ቤት፣ የሰጠንን ምክረ ሀሳብ […]

ባለፈው ዓመት ሕይወታቸው ያለፉ የአማራ ክልል ከፍተኛ መሪዎች የመታሰቢያ ሥነ ሥርዓት እየተካሄደ ነው።

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 15 ፣ 2012  ባለፈው ዓመት ሕይወታቸው ያለፉ የአማራ ክልል ከፍተኛ መሪዎች የመታሰቢያ ሥነ ሥርዓት እየተካሄደ ነው።በሥነ ሥርዓቱ የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ሌሎች የፌዴራልና የክልሉ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡ባለፈው ዓመት ሰኔ 15 በክልሉ በተፈጠረ የፀጥታ ችግር ሕይወታቸውን ላጡ የአማራ ክልል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና የፀጥታ ኃይሎች መታሰቢያ መርሀ ግብር እየተካሄደ […]

ዝክረ ሰኔ 15 የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ለተሰዉ ከፍተኛ አመራሮች 1ኛ ዓመት መታሰቢያ ተከናወነ ፡፡

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 15 ፣ 2012  ዝክረ ሰኔ 15 የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ለተሰዉ ከፍተኛ አመራሮች 1ኛ ዓመት መታሰቢያ ተከናወነ ፡፡በሰኔ 15 ቀን 2011ዓ.ም ለተሰዉ ከፍተኛ አመራሮች የ1ኛ አመት መታሰቢያ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ በን/ስ/ላፍቶ ክ/ከተማ ተካሂዷል። ምክትል ከንቲባ ኢንጅነር ታከለ ኡማ እና የአዲስ አበባ ብልፅግና ፓርቲ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋዬ በልጅጌ እንዲሁም […]

በጋዛ የሚገኙ አንድ ሚሊዮን ፍልስጤማዊያን ለከፋ የምግብ እጥረት ተጋልጠዋል ተባለ፡፡

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 15፣ 2012 በጋዛ የሚገኙ አንድ ሚሊዮን ፍልስጤማዊያን ለከፋ የምግብ እጥረት ተጋልጠዋል ተባለ፡፡ እስራኤል የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ለፍልስጤም ስደተኞች የሚልከውን ድጋፍ እንዳይደርስ በማገዷ በጋዛ የሚኖሩ አንድ ሚሊዮን የሚጠጉ ፍልስጤማዊያን ለምግብ እጥረት መጋለጣቸው ነው የተነገረው፡፡ አሜሪካ ለፍልስጤም ስደተኞች የሚሆን በዓመት 360 ሚሊዮን ዶላር የሚሆን እርዳታ ማቆሟ ደግሞ ጉዳቱን ያባባሰው ሌላኛው ጉዳይ መሆኑ ተጠቅሷል፡፡ የምግብ […]

የቀድሞ የኢፌድሪ ኤታማጆር ሹም ጀነራል ሰዓረ መኮንን የተሰዉበት አንደኛ አመት መታሰቢያ መርሀግብር ተከናወነ።

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 15፣ 2012 የቀድሞ የኢፌድሪ ኤታማጆር ሹም ጀነራል ሰዓረ መኮንን የተሰዉበት አንደኛ አመት መታሰቢያ መርሀግብር ተከናወነ።በመርሀግብሩ ላይ ኢ/ር ታከለ ኡማ እና የአዲስአበባ ብልጽግና ፓርቲ ሃላፊ አቶ ተስፋዬ በልጅጌ ተገኝተዋል።ጀነራል ሰዓረ ባለፈው አመት ህይወታቸው ከማለፉ ከሰዓታት በፊት ከኢ/ር ታከለ ኡማ ጋር በመሆን ከሩዋንዳ ወደ አትላስ በሚወስደው መንገድ ላይ ችግኝ በጋራ ተክለዋል።የመታሰቢያ መርሀግብሩ እየተከናወነ ያለውም […]