loading
እስራኤል በሁለት ዓመት ውስጥ አራተኛ ምርጫ ማካሄዷ የግድ ሆኖባታል ተባለ::

አዲስ አበባ፣ታህሳስ 14፣ 2013 እስራኤል በሁለት ዓመት ውስጥ አራተኛ ምርጫ ማካሄዷ የግድ ሆኖባታል ተባለ:: የጠቅላይ ሚንስትር ቤናሚን ኔታኒያሁና የአጣማሪያቸው ቤኒ ጋንትዝ የአንድነት መንግስት በገጠመው ፖለቲካዊ አለመረጋጋት ድንገቴ ምርጫ የማካሄድ ግዴታ ውስጥ ገብቷል፡፡ ባለፉት ሳምንታት የሀገሪቱ ምክር ቤት ፈርሶ አዲስ ምርጫ ይካሄድ የሚል ሀሳብ በህግ አውጭ አባላት መቅረቡን ተከትሎ ፓርላማው ፈርሷል ነው የተባለው፡፡ አልጀዚራ እንደዘገበው ምርጫው […]

በእንግሊዝና ፈረንሳይ መካከል ተጥሎ የነበረው የጉዞ እገዳ መነሳቱን ተከትሎ የትራንስፖርት አገልግሎቱ ዳግም ተጀምሯል፡፡

አዲስ አበባ፣ታህሳስ 14፣ 2013 በእንግሊዝና ፈረንሳይ መካከል ተጥሎ የነበረው የጉዞ እገዳ መነሳቱን ተከትሎ የትራንስፖርት አገልግሎቱ ዳግም ተጀምሯል፡፡ በእንግሊዝ አዲሱ የኮሮናቫይረስ በመከሰቱ በርካታ ሀገራት የጉዞ እቀባ መጣላቸውን የሚታወስ ሲሆን ፈረንሳይም አንዷ እንደነበር አይዘነጋም፡፡ አሁን ላይ ሀገራቱ በደረሱት ስምምነት መሰረት በእንግሊዝና ፈረንሳይ መካከል የሚደረጉ የባቡር ፣የአየርና የባህር ጉዞዎች ዳግም እንደሚጀመሩ ነው የተነገረው፡፡ የፈረንሳይ ዜጎችና በፈረንሳይ የሚኖሩ የእንግሊዝ […]

በመተከል ያለዉን የፀጥታ ችግር ከመሰረቱ ለመፍታት የተቀናጀ ኃይል እንዲሰማራ መደረጉን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ገለጹ፡፡

አዲስ አበባ፣ታህሳስ 15፣ 2013 በመተከል ያለዉን የፀጥታ ችግር ከመሰረቱ ለመፍታት የተቀናጀ ኃይል እንዲሰማራ መደረጉን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቤንሻንጉል ክልል በመተከል ዞን ያለዉ የጸጥታ ችግር በተለያየ መንገድ ለመፍታት የተቀናጀ ኃይል እንደሰማራ ተደርጓል ብለዋል፡፡ በቤንሻንጉል ክልል መተከል ዞን በዜጎች ላይ እየተፈፀመ ያለዉ ጭፍጨፋ እጅግ ኣሳዛኝ መሆኑን ጠቅላየሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡ በወገኖቻችን ላይ በተፈጸመዉ ኢሰባዊ ድርጊትም […]

በጋራ የድንበር አካባቢ በሱዳን በኩል የተደረጉ አዳዲስ ለዉጦችን የቀደሙ ስምምነቶችን የሚጥሱ በመሆናቸዉ በአስቸኳይ እንዲቆሙ ኢትዮጵያ አሳሰበች::

አዲስ አበባ፣ታህሳስ 15፣ 2013 በጋራ የድንበር አካባቢ በሱዳን በኩል የተደረጉ አዳዲስ ለዉጦችን የቀደሙ ስምምነቶችን የሚጥሱ በመሆናቸዉ በአስቸኳይ እንዲቆሙ ኢትዮጵያ አሳሰበች:: የጠቅላይ ሚኒስቴር ፕሬስ ሰክሬተርያት ጽ/ቤት ለአርትስ በላከዉ መረጃ እንዳስታወቀዉ፤ ሱዳን ከጥቅምት ወር መጨረሻ ጀምሮ ድንበር አካባቢ የቀደሙ ስምምነቶችን የሚጥሱ ፤እና መሬት ላይ ያለዉን እዉነታ የሚለዉጡ እንቅስቃሴዎችን እያደረገች እንደሆነና እንቅስቃሴዉ በአስቸኳይ እንደቆምና ወደቀደመዉ ቦታ እንዲመለስ የኢትዮጵያ […]

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሁለት ፓርቲዎችን ፈቃድ ሰረዘ፡፡

አዲስ አበባ፣ታህሳስ 20፣ 2013 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሁለት ፓርቲዎችን ፈቃድ ሰረዘ፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በታህሳስ 13 ቀን 2013 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ መሰረት ማሟላት ያለባቸው መስፈርቶች እንዲያሟሉ ከተጠየቁት መካከል አራት ፓርቲዎች መስፈርቱን ያሟሉ ሲሆን ሁለት ፓርቲዎች ደግሞ ባለሟሟላታቸው መሰረዛቸውን ገልጿል፡፡ የተጠየቀውን መስፈርት ያሟሉ ፓርቲዎች ፤የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር /ኦብነግ/- የአፋር ሕዝብ ፓርቲ /አሕፓ/፤ የጋሞ […]

በዳያስፖራው የተፈጠረው መነሳሳትና የአንድነት ስሜት ቀጣይነት እንዲኖረው ጥረት እየተደረገ ነው ተባለ::

አዲስ አበባ፣ታህሳስ 20፣ 2013 በዳያስፖራው የተፈጠረው መነሳሳትና የአንድነት ስሜት ቀጣይነት እንዲኖረው ጥረት እየተደረገ ነው ተባለ:: የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ኤጀንሲ እንዳስታወቀዉ የዳያስፖራዉ ማህበረሰብ በሀገር ልማትና ዕድገት ለማሳተፍ የሚያስችሉ ሥራዎች እየተሠሩ እንደሆነ ገልጿል፡፡ የዳያስፖራ የምክክር መድረክ በደቡብ አፍሪካ በተካሄደበት ወቅት የኤጀንሲዉ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሠላማዊት ዳዊት እንዳሉት ዳያስፖራው አባላት በንግድና ኢንስትመንት፣ በዕውቀት ሽግግር፣ በሬሚታንስና በሌሎች ወሳኝ የሀገር ልማት […]

በ2ኛው የዓለም ጦርነት የተሳተፉ የደቡብ አፍሪካ ወታደሮች ከ75 ዓመት በኋላ ውቅና አገኙ::

አዲስ አበባ፣ታህሳስ 20፣ 2013 በ2ኛው የዓለም ጦርነት የተሳተፉ የደቡብ አፍሪካ ወታደሮች ከ75 ዓመት በኋላ ውቅና አገኙ:: ወደ 80,000 የሚሆኑ ጥቁር ደቡብ አፍሪቃውያን እንደ የወታደራዊ ጓድ አካል ሆነው በጦርነቱ ቢሳተፉም ከነጭ ወታደሮች ያነሱ ተደርገው የእነሱ አስተዋፅዖ ሳይነገር ተዳፍኖ ቀርቶ ነበር፡፡ አሁን ግን በኮመንዌልዝ በኩል በተቋቋመው ኮሚሽን በወቅቱ ለተዋጉትና ለሞቱት እንዲሁም አሁንም በህይዎት ለሚገኙ ወታደሮች የመታሰቢያ ሂደት […]

በማዕከላዊ አፍሪካ ምርጫ በተከሰተ ብጥብጥ 800 የምርጫ ጣቢያዎች መዘጋታቸውን የሀገሪቱ የምርጫ ኮሚሽን አስታወቀ::

አዲስ አበባ፣ታህሳስ 20፣ 2013 በማዕከላዊ አፍሪካ ምርጫ በተከሰተ ብጥብጥ 800 የምርጫ ጣቢያዎች መዘጋታቸውን የሀገሪቱ የምጫ ኮሚሽን አስታወቀ:: የታጠቁ ሃይሎች ምርጫው በኪካሄድበት ወቅት ባደረሱት ጥቃት 14 በመቶ የሚሆኑት የምርጫ ጣቢያዎችን ለመዝጋት መገደዱን ነው ኮሚሽኑ የገለፀው፡፡ ታጣቂዎቹ በመራጮችና በምርጫ ሰራተኞች ላይ ጥቃት በመሰንዘር፣ እንዲሁም የምርጫ ኮሚሽኑ ስራውን እንዳያከናውን በማገድ ነው ሂደቱን ያደናቀፉት ተብሏል፡፡ የታጠቁ ሃይሎች በመራጮች ከማዋከብ […]

የተማሪዎችን የፈጠራ ውጤቶች በአግባቡ መምራት የሚያስችል ረቂቅ መመሪያ መዘጋጀቱ ተገለፀ::

አዲስ አበባ፣ታህሳስ 23፣ 2013 የተማሪዎችን የፈጠራ ውጤቶች በአግባቡ መምራት የሚያስችል ረቂቅ መመሪያ መዘጋጀቱ ተገለፀ:: የትምህርት ሚኒስቴር በሳይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በምህንድስና፣ በጥበብና ሂሳብ ዘርፍ የሚቀርቡ የተማሪዎችን የፈጠራ ስራዎች ከዚህ በፊት ከነበረው አሰራር ይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠል ረቂቅ መመሪያ ማዘጋጀቱን አስታውቋል፡፡ መመሪያው ተወዳዳሪዎች በተቀመጠላቸው መስፈርት መሰረት የፈጠራ ስራዎቻቸውን እንዲያቀርቡና አሸናፊዎች በማያሻማ መልኩ ተለይተው ተገቢውን ማበረታቻ እንዲያገኙ የሚያግዝ መሆኑ ነው […]

በጋምቤላ ክልል በሰለጠነ ባለሙያ የወለዱ እናቶች ሽፋን 40 በመቶ መሆኑ ተገለፀ::

አዲስ አበባ፣ታህሳስ 23፣ 2013 በጋምቤላ ክልል በሰለጠነ ባለሙያ የወለዱ እናቶች ሽፋን 40 በመቶ መሆኑ ተገለፀ:: በክልሉ የእናቶችና ጨቅላ ህፃናትን ጤናና የስርዓተ ምግብ ሁኔታን ለማሻሻል ያለመ የንቅናቄ መድረክ ተካሂዷል፡፡ በዚህ ወቅት የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ እንዳሉት በክልሉ በሰለጠነ ባለሙያ የሚወልዱ እናቶች ሽፋን 40 በመቶ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ሚኒስትሯ የህጻናት ክትባት መሻሻል ቢታይበትም አሁንም ዝቅተኛ ሽፋን እንዳለው […]