loading
የአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳን ግድያ ተከትሎ በኦሮሚያ ክልል በተከሰተ የፀጥታ መደፍረስ 123 ሰዎች ሲገደሉ 500 ሰዎች የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል ተባለ::

አዲስ አበባ፣ታህሳስ 23፣ 2013 የአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳን ግድያ ተከትሎ በኦሮሚያ ክልል በተከሰተ የፀጥታ መደፍረስ 123 ሰዎች ሲገደሉ 500 ሰዎች የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል ተባለ:: የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የምርመራውን ግኝቶች ይፋ ባደረገበት ወቅት በወንጀሉ የተሳተፉ ሰዎች ያደረሱት ጥቃት በሰብአዊነት ላይ የተፈጸመ ወንጀል ባሕርያትን የሚያሟሉ መሆናቸውን አረጋግጧል፡፡

እስራኤል በተጠናቀቀው የፈረንጆቹ 2020 በጋዛ ሰርጥ 300 ጥቃቶችን መፈፀሟን ይፋአደረገች::

አዲስ አበባ፣ታህሳስ 23፣ 2013 እስራኤል በተጠናቀቀው የፈረንጆቹ 2020 በጋዛ ሰርጥ 300 ጥቃቶችን መፈፀሟን ይፋአደረገች:: የሀገሪቱ መከላከለያ ተቋም ባወጣው መግለጫ በአካባቢው በተመረጡ 300 ኢላማዎችላይ ጥቃት ማድረሱንና 38 የጥቃት ሙከራዎችን ማክሸፉን ተናግሯል፡: ከጋዛ በኩል 176 ሮኬቶች ተተኩሰውብን ነበር ያለው የእስራኤል ጦር ሃይል ከነዚህ ውስጥ 90 በመቶ የሚሆኑት ባዶ ሜዳ ላይ ነው ያረፉት ብሏል፡፡ በሪፖርቱ እንደተገለፀው የእስራኤል ተዋጊ […]

አፍሪካ ሁለተኛው ዙር የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ጋር እየታገለች ነው ::

አዲስ አበባ፣ታህሳስ 23፣ 2013 አፍሪካ ሁለተኛው ዙር የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ጋር እየታገለች ነው ::ከቀሪው ዓለም ጋር ሲነፃፀር የበሽታው ስርጭት በአፍሪካ አነስተኛ ቢሆንም ከጊዜ ወደ ጊዜ ቁጥሩ እየጨመረ መምጣቱ ከፍተኛ ስጋትን ፈጥሯል፡፡ መረጃዎች እንደሚያሳዩት አሁን ላይ በ47 የአፍሪካ ሀገራት በበሽታው የተያዙባቸው ዜጎች ሳምንታዊ አማካይ ቁጥር 73 ሺህ መድረሱ ታውቋል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ በአፍሪካ አህጉር የበሽታውን የስርጭት መጠን […]

ተላላፊ በሽታዎችን ለመከላከል የጤና ኤክስቴንሽን ወሳኝ ሚና እያበረከተ መሆኑ ተገለጸ::

አዲስ አበባ፣ታህሳስ 26፣ 2013 ተላላፊ በሽታዎችን ለመከላከል የጤና ኤክስቴንሽን ወሳኝ ሚና እያበረከተ መሆኑ ተገለጸ:: የግልና አካባቢ ንጽህናን በአግባቡ በመጠበቅ የተላላፊ በሽታዎችን ስርጭት ለመቀነስ ለጤና ኤክስቴሽን ፕሮግራም የተሰጠው ትኩረት ውጤት እያመጣ መሆኑ ተገልጿል፡፡ የግልና የአካባቢ ንጽህናን ጨምሮ 19ኙ የጤና ኤክስቴንሽን ፓኬጆችን ተግባራዊ ያደረጉ ከ900 የሚበልጡ ግንባር ቀደም ቤተሰቦች ትናንት በባሌ ጎባ ተመርቀዋል። በግንባር ቀደም ቤተሰቦች ምረቃ […]

በኒጀር ፅንፈኛ ሃይሎች ባደረሱት ጥቃት ቢያንስ 100 ሰዎች መገደላቸው ተሰማ::

አዲስ አበባ፣ታህሳስ 26፣ 2013 በኒጀር ፅንፈኛ ሃይሎች ባደረሱት ጥቃት ቢያንስ 100 ሰዎች መገደላቸው ተሰማ:: በሀገሪቱ መንግስት አክራሪ የሚል ስያሜ የተሰጣቸው ቡድኖቹ ጥቃቱን ያደረሱት በማሊ ድንበር አቅራቢያ በሚገኙ በሁለት መንደሮች ነው ተብሏል፡፡ የኒጀር ጠቅላይ ሚኒስትር ጥቃቱ ወደ ተፈፀመባቸው መንደሮች በማቅናት የጎበኙ ሲሆን የተጎጂ ቤተሰቦችና ነዋሪዎቹን አበረታተዋል፡፡ ዩሮ ኒውስ እንደዘገበው ተዋጊ ሃይሎቹ ጥቃቱን ያደረሱት ሁለት ተዋጊ ሚሊሻዎቻቸው […]

ጃፓን የኮሮናቫይረስ መስፋፋትን ተከትሎ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ልትደነግግ ነው::

አዲስ አበባ፣ታህሳስ 26፣ 2013 ጃፓን የኮሮናቫይረስ መስፋፋትን ተከትሎ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ልትደነግግ ነው:: ጃፓን በሶስተኛው ዙር የኮቪድ 19 ወረርሽኝ ስረጭት አደጋ ውስጥ መሆኗን የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ተናግረዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዮሺሂንዴ ሱጋ በመግለጫቸው እንዳሉት አሁን ላይ ሀገሪቱ ያጋጠማትን የበሽታውን ስርጭት ስጋት ለመቀነስ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለመደንገግ እንገደዳለን ብለዋል፡፡ አልጀዚራ እንደዘገበው ጃፓን ከ4 ቀናት በፊት በ24 ሰዓታት […]

የላልይበላ ከተማ አስተዳደር የገና በዓል በሰላም እንዲጠናቀቅ አስፈላጊውን ዝግጅት አድርጌያለሁ አለ::

አዲስ አበባ፣ታህሳስ 28፣ 2013 የላልይበላ ከተማ አስተዳደር የገና በዓል በሰላም እንዲጠናቀቅ አስፈላጊውን ዝግጅት አድርጌያለሁ አለ:: የደብረ ሮሃ ቅዱስ ላልይበላ ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም እንዲጠናቀቅ አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት ተደርጎ እየተሠራ መሆኑን ነው የከተማ አስተዳደሩ የገለፀው፡፡ የቅዱስ ላልይበላን ዓመታዊ ክብረ በዓል ምዕምናንና ጎብኚዎች ወደ ሥፍራው መግባት ከጀመሩ ቀናት ተቆጥረዋል። ቅድስቲቷ ምድርም በምዕመናንና በጎብኝዎች ተውባለች። የበዓሉን ዝግጅት አስመልክቶ […]

ሴት አመራሮች የላቀ የአመራር ጥበብና በውሳኔ አሰጣጥ የተግባቦታዊ ኪሂል በመጎናፀፍ ተቋማቸውን በብቃት ሊመሩ እንደሚገባ ተገለፀ ፡፡

አዲስ አበባ፣ጥር 03፣ 2013 ሴት አመራሮች የላቀ የአመራር ጥበብና በውሳኔ አሰጣጥ የተግባቦታዊ ኪሂል በመጎናፀፍ ተቋማቸውን በብቃት ሊመሩ እንደሚገባ ተገለፀ ፡፡ በከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር አዘጋጅነት ከሁሉም የፌደራል ተቋማት ለተውጣጡ ሴት ሚኒስትሮች፣ ሴት ሚኒስቴር ዴኤታዎች፣ ሴት የፓርላማ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዎች፣ ኮሚሽነሮችና በከፍተኛ ሴት አመራር ደረጃ ለሚገኙ አካላት የአመራር ጥበብና ተግባቦታዊ ክሂላቸውን የሚያዳብሩበት ስልጠናና እርስ በርሳቸው የካበተ […]

በመላዉ ዓለም የኮቪድ 19 ክትባት መሰጠት መጀመሩ ኢትዮጵያን ከቫይረሱ እንዳይጠነቀቁ ሊያደርግ አይገባም::

አዲስ አበባ፣ጥር 03፣ 2013 በመላዉ ዓለም የኮቪድ 19 ክትባት መሰጠት መጀመሩ ኢትዮጵያን ከቫይረሱ እንዳይጠነቀቁ ሊያደርግ አይገባም ሲሉ አርትስ ያነጋገራቸዉ በሚሊኒየም የኮቪድ 19 ኬር ሴንተር የነርስኒግ ዳይሬክተር ሲስተር ንጋት ወ/ማርያም አሳሰቡ ፡፡ በማዕከሉ ቀደም ሲል ከነበረዉ የታማሚዎች ቁጥርና የፅኑ ህክምና  የሚያስፈልጋቸዉ ሰዎች ቁጥር መበራከታቸዉን ያስታወሱት ሲስተር ንጋት ፤የኮቪድ 19 ክትባት ቢገኝም ለአፍሪካ ብሎም ለኢትዮጵያ ተዳራሽ የመሆኑ […]

ኬንያ እና ሶማሊያ አሁንም በመልካም ጉርብትናቸው የሚቀጡሉበት መንገድ አልተዘጋም ተባለ::

አዲስ አበባ፣ጥር 03፣ 2013 ኬንያ እና ሶማሊያ አሁንም በመልካም ጉርብትናቸው የሚቀጡሉበት መንገድ አልተዘጋም ተባለ:: ሶማሊያ ባለፈው ዲሴምበር ወር በውስጥ ጉዳዬ ጣልቃ ገባችብኝ በሚል መነሻ ከኬንያ ጋር የዲፕሎማሲ ግንኙነቷን በይፋ አቋርጣለች፡፡ ሁለቱ ሀገራት ግንኙነታቸው ወደ ነበረበት እንዲመለስ ተደጋጋሚ ጥረት ሲያደርጉ የአፍሪካ ህብረትም ውዝግቡ በሰላም እንዲፈታ አሳስቦ ነበር፡፡ ሶማሊያ ውስጥ በአስር ሽዎች የሚቆጠሩ ኬንያዊያን ሰራተኞች እንዳሉና በኬንያም […]