loading
ቱኒዚያዊያን በመንግስት ላይ የጀመሩት ተቃውሞ ከአራት ቀናት በላይ አስቆጥሯል::

አዲስ አበባ፣ጥር 12፣ 2013 ቱኒዚያዊያን በመንግስት ላይ የጀመሩት ተቃውሞ ከአራት ቀናት በላይ አስቆጥሯል:: ተቃዋሚዎቹ ጎዳናዎችን በመዝጋትና ቁሳቁሶችን በእሳት በማቀጣጠል ቁጣቸው በአደባባይ ሲያሰሙ ታይተዋል፡፡ የተቃውሟቸው መነሻ በሀገሪቱ የተንሰራፋው ድህነትና የስራ አጥነት መባባስ መሆኑን ለተቃውሞ በወጡበት ወቅት ገልፀዋል፡፡ አልጀዚራ በዘገባው እንዳስነበበው ሰልፈኞቹ የተለያዩ ሱቆችንና የንግድ ተቋማትን በመዝረፍ ተግባር ላይ መሰማራታቸውም ተሰምቷል፡፡ ይህን ተከትሎም የቱኒዚያው ፕሬዚዳንት ካይስ ሰይድ […]

ኢራን በሁለት ሳምንታት ውስጥ ሁለት ወታራዊ ልምምዶችን ማድረጓ ተሰማ፡፡

አዲስ አበባ፣ጥር 12፣ 2013 ኢራን በሁለት ሳምንታት ውስጥ ሁለት ወታራዊ ልምምዶችን ማድረጓ ተሰማ፡፡ የአሜሪካ ቢ 52 ቦንብ ጣይ አውሮፕላኖች በመካከለኛው ምስራቅ መብረራቸውን ተከትሎ ቴህራን በሀገሪቱ ደቡባዊ ጠረፍ አካባቢ ከባድ ልምምዶችን አድርጋለች ነው የተባለው፡፡ አልጀዚራ እንደዘገበው ባለፈው ጃኑዋሪ 3 በጄኔራል ቃሲም ሰይማኒ ላይ ግድያ ከተፈፀመ ወዲህ የአሜሪካ ቦንብ ጣይ አውሮፕላኖች በአካባው ሲበሩ የመጀመሪያቸው ነው፡፡ ኢራን በሁለት […]

ግብፅ በመላ ሀገሪቱ ጣለችውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለአስራአምስተኛ ጊዜ አራዘመች::

አዲስ አበባ፣ጥር 16፣ 2013  ግብፅ በመላ ሀገሪቱ ጣለችውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለአስራአምስተኛ ጊዜ አራዘመች:: በቀጣዮቹ ሶስት ወራት ተግባዋ የሚሆነው የአስቸኳይ ጊዜ አቃጅ ዳግም የታደሰው በፓርላመው ውሳኔና በፕሬዚዳንት አብደልፈታህ አልሲሲ ይሁንታ ነው፡፡ ሚድል ኢስት ሞኒተር እንደዘገበው ግብፅ የመጀመሪያውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የጣለቸው እንደ አውሮፓዊያኑ አቆጣጠር በ2017 ነበር፡፡ በወቅቱ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የተደነገገው የሽበርተኝነትን አደጋ ለመከላከል በሚል […]

የሊቢያ ተፋላሚ ኃይሎች ስምምነት

አዲስ አበባ፣ጥር 17፣ 2013  የሊቢያ ተፋላሚ ኃይሎች ቁልፍ የመንግስት ተቋማትን የሚመሩ እጩዎችን ለመምረጥ ተስማሙ ::የሁለቱም ወገኖች ተወካዮች ሞሮኮ ላይ ባደረጉት አዲስ ውይይት የእጩዎቹ የምልመላ ሂደት ከማክሰኞ ጀምሮ እንደሚከናወን አስታውቀዋል፡፡ ተፋላሚ ሃይሎቹ የደረሱበት ስምምነት በሀገሪቱ ለአስር ዓመታት የተካሄደውን የእርስ በርስ ጦርነት እንዲያበቃ ለማድረግ ሁነኛ መፍትሄ መሆኑ ነው የተመገረለት፡፡ ሂደቱ እስከመጭው ፌብሩዋሪ 2 ቀን ድረስ የሚጠናቀቅ ሲሆን […]

በሩሲያ የተቀሰቀሰው ህዝባዊ ተቃውሞ::

አዲስ አበባ፣ጥር 17፣ 2013 በሩሲያ የተቀሰቀሰው ህዝባዊ ተቃውሞ:: የሩሲያ የፀጥታ ሃይሎች ከ3 ሺህ በላይ ተቃዋሚ ሰልፈኞችን ማሰራቸው ተሰማ ሰልፈኞቹ አደባባይ የወጡት በቅርቡ ከህመም ያገገሙት የተቃዋሚ መሪው አሌክስ ናቫልኒ ከእስር ይፈቱልን የሚል ጥያቄ ይዘው ነው፡፡

በእንግሊዝ በሙከራ ሂደት ላይ ያለው የኮቪድ-19 ክትባት መልካም ውጤት እያሳየ ነው ተባለ፡፡

አዲስ አበባ፣ጥር 21፣ 2013 በእንግሊዝ በሙከራ ሂደት ላይ ያለው የኮቪድ-19 ክትባት መልካም ውጤት እያሳየ ነው ተባለ፡፡ የክትባቱ የውጤታማነት ደረጃ ሲለካ 89 ነጥብ 3 በመቶ እንደሆነ የእንግሊዝ የጤና ባለሙያዎች ይፋ ማድረጋቸው ተሰምቷል፡፡ ቢቢሲ እንደዘገበው ጠቅላይ ሚኒስትር ቦሪስ ጆንሰን ይህን መልካም ዜና እንደሰሙ የተሰማቸውን ደስታ ገልፀዋል፡፡ ኖቫቫክስ የተባለው ይህ ክትባት አዲሱን የኮሮናቫይረስ ዝርያ በመከላከል ውጤታማ ሆኖ የተገኘ […]

የማዕከላዊ አፍሪካ ዜጎች ወደጎረቤት ዲሞክራቲክ ኮንጎ መጠለያ ፍለጋ እየተሰደዱ ነው ተባለ፡፡

አዲስ አበባ፣ጥር 21፣ 2013 የማዕከላዊ አፍሪካ ዜጎች ወደጎረቤት ዲሞክራቲክ ኮንጎ መጠለያ ፍለጋ እየተሰደዱ ነው ተባለ፡፡ ስደተኞቹ ቀያቸውን ጥለው የሚሰደዱት በሀገሪቱ ነፍጥ አንግበው ከሚዋጉ ሚሊሻዎች ጥቃት ህይዎታቸውን ለማዳን ሲሉ ነው፡፡ አፍሪካ ኒውስ እንደዘገበው በአሁኑ ወቅት ከማዕከላዊ አፍሪካ ወደ ጎረቤትረ ዲሞክራቲክ ኮንጎ የተሰደዱ 30 ሺህ ዜጎች በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ይኖራሉ፡፡ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ መስሪያ ቤት […]

አይቤክስ ኮሌጅ ከፍለው መማር ለማይችሉ 150 ዜጎች ነፃ የትምህርት ዕድል ተጠቃሚ ማድረጉን አስታወቀ፡፡

አዲስ አበባ፣ጥር 24፣ 2013 አይቤክስ ኮሌጅ ከፍለው መማር ለማይችሉ 150 ዜጎች ነፃ የትምህርት ዕድል ተጠቃሚ ማድረጉን አስታወቀ፡፡ ኮሌጁ ከተቋቋመ ከ2002 ጀምሮ በሆቴል እና ቱሪዝም ዘርፍ ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር መጀመሩን ያስታወሱት የኮሌጁ ዲን አቶ ተስፍዬ አሰፋ ፤ እስካሁን ድረስ ከፍለው መማር ለማይችሉ 150 ዜጎች ነፃ የትምህርት ዕድል በመስጠት ወደ ስራ ማስግባታቸውን ተናግረዋል። በዘንድሮው ዓመት በሆቴል ማኔጅመንት […]

ሞቃዲሾ ውስጥ የደረሰ የቦንብ አደጋ የሞትና የአካል ጉዳት አድርሷል ተባለ::

አዲስ አበባ፣ጥር 24፣ 2013 ሞቃዲሾ ውስጥ የደረሰ የቦንብ አደጋ የሞትና የአካል ጉዳት አድርሷል ተባለ:: አደጋው የተፈፀመው በማዕከላዊ ሞቃዲሾ በሚገኘው አፍሪክ ሆቴል ላይ ሲሆን ታጣቂዎች በአካባቢው ሁከት ከፈጠሩ በኋላ ፍንዳታው መከተሉን የዓይን እማኞች ተናግረዋል፡፡ በአደጋው ሳቢያ አንድ ጡረተኛ የጦር ጄኔራልን ጨምሮ አምስት ሰዎች ህይዎታቸው ማለፉ ተሰምቷል፡፡ ከሟቾቹ በተጨማሪ 10 ሰዎች በአደጋው ምክንያት የመቁሰል አደጋ እንደደረሰባቸው አፍሪካ […]

ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ሁለት አዳዲስ የህግ ጠበቆችን መቅጠራቸው ተሰማ::

አዲስ አበባ፣ጥር 24፣ 2013 ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ሁለት አዳዲስ የህግ ጠበቆችን መቅጠራቸው ተሰማ:: የቀድሞው ፕሬዚዳንት በስልጣን ላይ በነበሩበት ወቅት ህግ ተላልፈዋል መባላቸውን ተከትሎ ክስ ስለሚጠብቃቸው ራሳቸውን ለመከላkል ነው ይህን ያደረጉት ተብሏል፡፡ ትራምፕ ከሚጠብቃቸው ክስ ይከላከሉልኛል ያሏቸውን ዴቪድ ሾን እና ብሩስ ካስቶር የተባሉ የህግ ጠበቆችን መቅጠራቸውን ይፋ አድርገዋል፡፡ ትራምፕ አዳዲስ ጠበቆችን ለመቅጠር የተገደዱት የቀድሞዎቹ ጠበቆቻቸው ከሳቸው […]