loading
በዘንድሮው ዓመት 5 ቢሊዮን ችግኝ ለመትከል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ ገለጹ::

በዘንድሮው ዓመት 5 ቢሊዮን ችግኝ ለመትከል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ ገለጹ:: ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን የገለጹት ዘንድሮ የሚተከሉ ችግኞች ያሉበትን ደረጃ በጎበኙበት ወቅት ነዉ፡፡ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኦሮሚያ ክልል ሶደሬ አካባቢ በመገኘት ነው የችግኝ ማፍላት ስራውን ከክልሉ ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ ጋር በመሆን የጎበኙት።በዘንድሮው አመት 5 ቢሊዮን ችግኝ ለመትከል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የገለፁት ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ፥ […]

ማንኛዉም ሰዉ ደም ለመለገስ ሲመጣ ፕሮግራም አሲዞ እንዲመጣ የሚያደርግ መተግበሪያ እየተዘጋጀ መሆኑን የቢሄራዊ ደም ባንክ አስታወቀ፡፡

አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 16 ፣ 2012 ማንኛዉም ሰዉ ደም ለመለገስ ሲመጣ ፕሮግራም አሲዞ እንዲመጣ የሚያደርግ መተግበሪያ እየተዘጋጀ መሆኑን የቢሄራዊ ደም ባንክ አስታወቀ፡፡የደም ባንኩ ኮሮና ቫይረስ በኢትዮጵያ ከተከሰተ የመጀመሪያዎቹ ሳምንታት ላይ የደም እጥረት ነበረ አሁን ላይ ግን በተሰራዉ የግንዛቤ ማስጨበጫ ታላቅ መነቃቃት መታየቱን ያስታወቀ ሲሆን የረመዳንን ፆም ምክንያት በማድረግ ሁሉም የብሄራዊ ደም ባንክ ቅርጫፎች እስከ […]

በኢትዮጵያ ከኮሮና ቫይረስ ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 50 ደረሰ

አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 19 ፣ 2012 በኢትዮጵያ ከኮሮና ቫይረስ ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 50 ደረሰ በኢትዮጵያ ከኮሮና ቫይረስ ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 50 መድረሱን የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ አስታወቁ።ሚኒስትሯ ባለፉት 24 ሰዓታት ለ943 ሰዎች የላቦራቶሪ ምርመራ መደረጉን በፌስ ቡክ ገጻቸው የገለጹ ሲሆን፤በዚህም አንድ ሰው የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶበታል፡፡ቫይረሱ የተገኘበት የ45 አመት ትውልደ ኢትዮጵያዊ የእንግሊዝ ዜግነት ያለው […]

የኮሮና ቫይረስ ትምህርት ላይ ሊያስከትል የሚችለውን ተፅዕኖ ለመከላከል የፖሊሲ ምክረ ሀሳብ ለማዘጋጀት ስምምነት ላይ ተደረሰ::

አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 19 ፣ 2012 የኮሮና ቫይረስ ትምህርት ላይ ሊያስከትል የሚችለውን ተፅዕኖ ለመከላከል የፖሊሲ ምክረ ሀሳብ ለማዘጋጀት ስምምነት ላይ ተደረሰ:: የትምህርት የወደፊት ዕጣ ፈንታን የሚመለከተው ዓለም አቀፉ የባህል ተቋም ዩኔስኮ ዓለም አቀፍ ኮሚሽንን 2ኛ ስብሰባ ተካሂዷል።በዚህም ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅን ጨምሮ የሚመለከታቸው አካላት ተሳታፊ ሆኖነዋል።በውይይቱም የኮረሮ ቫይረስ በትምህርትና ልማት ላይ በረጅም ጊዜ ሊያስከትል የሚችለውን ተፅዕኖ […]

“ፈጠራ በቀውስ ጊዜ” የአዲስ ወግ ዌቢነር ውይይት በቪዲዮ ኮንፈረንስ ተካሄደ::

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 20፣ 2012 “ፈጠራ በቀውስ ጊዜ” የአዲስ ወግ ዌቢነር ውይይት በቪዲዮ ኮንፈረንስ ተካሄደ:: በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አዘጋጅነት በተካሄደዉ ዉይይት  በቀውስ ጊዜ የሚፈጠሩ አዳዲስ ችግሮችን ማለፍ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ አተኩሯል፡፡ችግር ለፈጠራ መንስኤ በመሆኑ ችግር ፈቺ ፈጠራዎች ላይ ትኩረት ሊደረግ እንደሚገባ የቪዲዮ ኮንፈረንሱ አወያይ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ ዶክተር አብርሃም በላይ ተናግረዋል።ሁሉም ስብሰባዎች በቪዲዮ ኮንፈርንስ እንዲደረጉ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሩ፤ ውይይቶች በቪዲዮ ኮንፈረንስ አማካይነት እየተካሄዱና በቀጣይ የበለጠ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የሚደረግ መሆኑን አመልክተዋል። ኢትዮጵያ ወደ ዲጂታል ኢኮኖሚ እንድትሸጋገር የሚያግዙ የፖሊሲና የህግ ማዕቀፍ እንዲጸድቅ እየተሰራ እንደሆነም ጠቁመዋል።የኢ-ኮሜርስ፣ ኢ-ሰርቪስ፣ የኢ፤ትራንዛክሽን አዋጅ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ጸድቆ ለህዝብ ተወካዮች መላኩንም ተናግረዋል።እነዚህን አገልግሎቶች በፍጥነት ስራ ላይ ለማዋል እየተሰራ ሲሆን ከ30 በላይ በቴክኖሎጂ ላይ የሚሰሩ ተቋማት ያላቸውን የቴክኖሎጂናአማራጭ እንዲያቀርቡ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።የመንግስት ተቋማትን እናአገልግሎት ፤ሰዎች በያሉበት ሆነው ለማግኘት እንዲችሉ “የኢ-ሰርቪስ” አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል ስራ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።የኮሮናቫይረስን ለመከላከል የሚያስችል የፈጠራ ስራ እየሰሩ ያሉ ሰዎች ለሚኒስቴሩ እንዲያቀርቡ እና እውቅና እንዲያገኙ ሁኔታዎች መመቻቸቱንም ጠቁመዋል።

 ባለስልጣኑ  ሰባት መንገዶችን በአስፓልት ደረጃ ለመገንባት የሚያስችል የውል ስምምነት አካሔደ።

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 20፣ 2012 ባለስልጣኑ  ሰባት መንገዶችን በአስፓልት ደረጃ ለመገንባት የሚያስችል የውል ስምምነት አካሔደ። የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን ከ11 ነጥብ ስድስት ቢሊየን ብር በላይ በሆነ ወጭ ሰባት መንገዶችን በአስፓልት ደረጃ ለመገንባት የሚያስችል የውል ስምምነት ማከሄዱን የትራንስፖርት ሚኒስቴር አስታዉቋል፡፡የውል ስምምነት የተፈረመላቸው ሰባት መንገዶች በጥቅሉ ከ500 ኪ.ሜ በላይ ርዝመት አላቸው።ለግንባታቸው የሚውለው ገንዘብ ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያ መንግሥት የሚሸፈን መሆኑ […]

በዲሞክራቲክ ኮንጎ ለአራት ቀናት በተካሄደ የእርስ በርስ ግጭት 43 ሰዎች መሞታቸው ተነገረ፡፡

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 20፣ 2012 በዲሞክራቲክ ኮንጎ ለአራት ቀናት በተካሄደ የእርስ በርስ ግጭት 43 ሰዎች መሞታቸው ተነገረ፡፡አጃንስ ፍራንስ ፕረስ የወታደር ባለስልጣናትን ምንጭ ጠቅሶ እንደዘገበው በሀገሪቱ ምስራቃዊ ክፍል በሚገኙ ሁለት ግዛቶች በተፈጠረ ግጭት 43 ሰዎች ህይወታቸውን አጥተዋል፡፡በግጭቱ አርብ እለት ጥቃት አድራሾች ስለትና የጦር መሳሪያ በመጠቀም 21 ንጹሃን ሰዎችን መግደላቸውን ነው አጃንስ ፍራንስ ፕረስ የዘገበው፡፡ በድንበር አቅራቢያ […]

ኮቪድ19 ምርጫን ማራዘም እና “ የህግ አማራጮች” በሚል ርዕስ ውይይት ተካሄደ::

አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 21 ፣ 2012 ኮቪድ19 ምርጫን ማራዘም እና “ የህግ አማራጮች” በሚል ርዕስ ውይይት ተካሄደ::በኮቪድ19 ምክንያት ቀጣዩን ምርጫ ለማካሄድ አስቸጋሪ በመሆኑ መንግስት አራት የመፍትሄ አማራጮችን አቅርቧል።“ኮቪድ19 ምርጫን ማራዘም እና የህግ አማራጮች” በሚል ርዕስ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት መንግስት ከተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር  ነዉ ውይይት ያካሄደዉ፡፡ ኢትዮጵያ በህገ መንግስቱ መሰረት እስከ ነሃሴ […]

የቱርክ መንግስት ለኮቪድ -19 ወረርሽኝ መከላከል ተግባር የሚውሉ ቁሳቁሶችን ድጋፍ አደረገ::

አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 21 ፣ 2012 የቱርክ መንግስት ለኮቪድ -19 ወረርሽኝ መከላከል ተግባር የሚውሉ ቁሳቁሶችን ድጋፍ አደረገ:: የቱርክ መንግስት ለኮቪድ -19 ወረርሽኝ መከላከል ተግባር የሚውሉ  ድጋፍ ያደረጉ የተለያዩ ቁሳቁሶችን ለኢ.ፌ.ዴ.ሪ የሴቶች፣ ሕጻናትና ወጣቶች ሚኒስቴር አስረክቧል፡፡ድጋፉ በዋነኝነት ለኮቪድ 19 በሽታ መከላከያ ተግባር የሚውሉ ሲሆን 280 ካርቶን ወይም 1 ሺህ 700 ኪሎ ግራም የሆነ የንጽሕና መጠበቂያ ቁሳቁሶች፣ […]

ሞሮኮ በማረሚያ ቤቶቿ ባደረገችው ምርመራ ከ300 በላይ ታራሚዎች በኮቪድ 19 መያዛቸውን አረጋገጠች::

አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 21 ፣ 2012 ሞሮኮ በማረሚያ ቤቶቿ ባደረገችው ምርመራ ከ300 በላይ ታራሚዎች በኮቪድ 19 መያዛቸውን አረጋገጠች:: ይሄ ቁጥር የተገኘው በሶስት እስር ቤቶች በሚገኙ 1 ሺህ 736 እስረኞች ላይ በተደረገ ምርመራ መሆኑን አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ በዘገባው አስነብቧል፡፡ከነዚህ ሶስት እስር ቤቶች መካከል ደግሞ 303 በኮሮና ቫይረስ የተያዙት ሰዎች የተገኙት በሀገሪቱ ደቡባዊ ክፍል በሚገኝ ኦዋራዛቴ […]