loading
በዉጪ የሚገኙ ትውልደ  ኢትዮጵያዉያን ኮሮና ቫይረስን ለመከላከል የሚዉል ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ ድጋፍ አደረጉ ፡፡

በዉጪ የሚገኙ ትውልደ  ኢትዮጵያዉያን ኮሮና ቫይረስን ለመከላከል የሚዉል ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ ድጋፍ አደረጉ ፡፡ አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 28 ፣ 2012 በተለያዮ የዓለም ሀገራት የሚገኙ ትውልደ ኢትዮጵያዉያን እንዲሁም ከሚሲዮኖች ሰራተኞች ከ100 ሚሊዮን ብር  በላይ መሰብሰቡን የብሄራዊ ድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴ አስታዉቋል፡፡ድጋፉ ባለፉት ጥቂት ሳምንታት በውጭ በሚገኙ 60 ሚሲዮኖች መሰባሰቡ ተጠቁሟል፡፡ ድጋፉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አቶ ገዱ እንዳርጋቸው ተረክበዋል።ሚኒስትሩ በዚህ  ወቅት ድጋፉ አገር በችግር ውስጥ ባለችበት ጊዜ በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ያደረጉት በመሆኑ አመስግነዋል። በተለይ ራሳቸው ችግር ውስጥ ሆነው አገራቸውን እየረዱ ያሉ ወገኖች እንዲሁም ሚሲዮኖች እያደረጉ  ላለው  ድጋፍ  አድናቆታቸውን ገልጸዋል።በሀገር ዉስጥ የሚገኙ ባለሀብቶች ይሁን በዉጪ የሚገኙ ትውልደ ኢትዮጵያዉያን  ቫይረሱን ለመከላከል በሚደረገዉ ጥረት […]

የትራንስፖርት ሚኒስትር ወይዘሮ ዳግማዊት ሞገስ የመናኸሪያ አገልግሎት አሰጣጥን ጎበኙ::

አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 28 ፣ 2012 የትራንስፖርት ሚኒስትር ወይዘሮ ዳግማዊት ሞገስ የመናኸሪያ አገልግሎት አሰጣጥን ጎበኙ:: የትራንስፖርት ሚኒስትሯ ወይዘሮ ዳግማዊት ሞገስ የመናኸሪያ አገልግሎት አሰጣጥንና የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከል እየተሰራ ያለውን ስራ በማለዳ ጎብኝተዋል። የአስኮ፣ የመርካቶና የአየር ጤና መናኸሪያዎች የአገልግሎት አሰጣጥን ነዉተዘዋውረው የተመለከቱት በጉብኝታቸውም ተገልጋዮችን ሹፌሮችና ሌሎችንም የኮቪድ-19 ወረርሽኝን ስርጭት ለመከላከል ስለሚያደርጉት ጥንቃቄና ሌሎች ተዛማጅ ጉዳዮችን በተመለከተ የአነጋግረዋል።በተለይ በአገሪቱ የኮቪድ 19 ቨይረስን ለመከላከል በትራንስፖርት ውስጥ እየተደረገ ያለውን ጥንቃቄና የኬሚካል ርጭት ተመልክተዋል።የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ለማስፈጸም በወጣዉ ድንጋጌ የሚኒስትሮች ኮሚቴ የትራንስፖርት ዘርፍ አፈፃጸም መመሪያ አውጥቶ ወደ ስራ መግባቱ ይታወሳል።

ደቡብ አፍሪካ የቲቢ ክትባትን ኮቪድ 19ን ለመከላከል  ይውል ዘንድ ሙከራ መጀመሯን ይፋ አደረገች፡፡

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 28፣ 2012 ደቡብ አፍሪካ የቲቢ ክትባትን ኮቪድ 19ን ለመከላከል  ይውል ዘንድ ሙከራ መጀመሯን ይፋ አደረገች፡፡የጤና ባለሙያዎች ለኮቪድ 19 ክትባት ለማግኘት የምርመርና የሙከራ ስራ በመስራት መጠመዳቸው ነው የተነገረው፡፡አምስት መቶ የጤና ባለሙያዎች ለዚሁ ስራ የተመደቡ ሲሆን የክሊኒካል የምርመር ተቋማት ደግሞ የምርምር ስራዉን በገንዘብ ይደግፋሉ ተብሏል፡፡በኬፕታውን  ክትባቱ የሚሞከርባቸው 3ሺ በጎ ፈቃደኛ ሰዎች ተዘጋጅተው ለአንድ ዓመት […]

ናይጄሪያ የእንቅስቃሴ እገዳ ባነሳች በሰዓታት ውስጥ የታማሚዎች ቁጥር በ245 መጨመሩ ድንጋጤን ፈጥሮባታል::

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 28፣ 2012 ናይጄሪያ የእንቅስቃሴ እገዳ ባነሳች በሰዓታት ውስጥ የታማሚዎች ቁጥር በ245 መጨመሩ ድንጋጤን ፈጥሮባታል::የሀገሪቱ የበሽታዎች መቆጣጠሪያ ማዕከል እንዳለው በናይጄሪያ ከአሁን በፊት በአንድ ቀን ውስጥ ይሄን ያህል በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ተመዝግበው አያዉቁም፡፡ናይጄሪያ ለስድት ሳምንታት ያህል ጥላው የቆየችውን የእንቅስቃሴ እገዳ ያላላችው የበሽታው ስርጭት የመቀነስ አዝማሚያ በማየቱ ነበር፡፡ይሁን እንጂ ተዘግተው የነበሩ የንግድ እና ሌች አገልግሎት […]

በጥቂት ዓመታት በመላው ኢትዮጵያ 20 ቢሊዮን ችግኞች  እንደሚተከሉ  ጠቅላይ ሚኒሰትር ዐቢይ ተናገሩ፡፡

በጥቂት ዓመታት በመላው ኢትዮጵያ 20 ቢሊዮን ችግኞች  እንደሚተከሉ  ጠቅላይ ሚኒሰትር ዐቢይ ተናገሩ፡፡ አዲስ አበባ፣ ግንቦት 5፣ 2012 ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት፣ የዚህን ዓመት የ አረንጓዴ አሻራ   የችግኝ ተከላ ቅድመ ዝግጅት በተመለከተ የግብርና ሚኒስቴር ማብራሪያ አቅርቧል፡፡የብሔራዊ አስተባባሪ ኮሚቴው አባላት፣ የቴክኒክ ኮሚቴ አባላት፣ የክልል ፕሬዚደንቶች፣ ሕዝቡን የማነሳሳት ሥራን የሚከውኑ ተጽዕኖ አሳዳሪ ግለሰቦችን ጨምሮ ዐበይት ባለድርሻ አካላት ተሳትፈውበታል፡፡ባለፈው […]

በአዲስ አበባ የአፍ እና አፍንጫ መሸፈኛ ጭንብል ያላደረጉ ሰዎችን ማሰር መጀመሩን ፖሊስ አስታወቀ ።

በአዲስ አበባ የአፍ እና አፍንጫ መሸፈኛ ጭንብል ያላደረጉ ሰዎችን ማሰር መጀመሩን ፖሊስ አስታወቀ ። አዲስ አበባ፣ ግንቦት 5፣ 2012  የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን  እንዳለው በአስቸኳይ አዋጁ መሰረት ለኮሮና ቫይረስ መከላከያ የአፍ እና አፍንጫ መሸፈኛ ጭንብል ሁሉም ሰው የግድ መጠቀም ባለበት ሰዓት እንዲጠቀም ያስገድዳል።በዚህም መሰረት የአፍ እና አፍንጫ መሸፈኛ ጭንብልጭንብል ያላደረጉ ሰዎች በፖሊስ በመታሰር ላይ ናቸው።የኮሚሽኑ […]

በኢትዮጵያ ወጣቶች ለኮሮና ቫይረስ ይበልጥ ተጋላጭ መሆናቸዉን የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዮትአስታወቀ፡፡

በኢትዮጵያ ወጣቶች ለኮሮና ቫይረስ ይበልጥ ተጋላጭ መሆናቸዉን የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዮትአስታወቀ፡፡ አዲስ አበባ፣ ግንቦት 5፣ 2012  ኢንስቲትዩቱ እንዳስታወቀዉ በኢትዮጵያ አስከ ማክሰኞ ዕለት በኮሮና ቫይረስ ከተያዙ 261   ሰዎች መካከል 91 የሚሆኑት እድሜያቸዉ ከ15- 24 ዓመት መሆኑን የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዮት ያወጣዉ አህዛዊ መረጃ ይጠቁማል፡፡ከ25 -34 ባሉት የእድሜ ክልል ዉስጥ ያሉት ደግሞ በሁለተኛ ደረጃ ተጋላጭ  መሆናቸዉን ነዉ መረጃዉ ያመላከተዉ […]

ጀርመን የኮሮና ወረርሽኝን ለመከላከል የቁሳቁስ ድጋፍ አደረገች::

ጀርመን የኮሮና ወረርሽኝን ለመከላከል የቁሳቁስ ድጋፍ አደረገች:: አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 5 ፣ 2012 የጀርመን መንግሥት በኢትዮጵያ የኮሮና ወረርሽኝን ለመከላከል የቁሳቁስ ድጋፉን ለሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር አስረክቧል።ድጋፉ በኢትዮጵያ የኮሮና ወረርሽን ለመከላከል ተግባራዊ ካደረጋቸው የድጋፍ ማዕቀፎች መካከል አንዱ  መሆኑ ተገልጿል።በኢትዮጵያ የጀርመን አምባሳደር ብሪታ ዋግነር ለሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትሯ ፕሮፌሰር ሒሩት ወልደማሪያም ነዉ ድጋፉን ያስረከቡት ፡፡ቫይረሱ በዓለም ላይ ጉዳት እያደረሰ መሆኑን  ያስታወሱት አምባሳደሯ፤አገራቸው ኢትዮጵያን ለመርዳት ድጋፉን ማድረጓን ገልጸዋል። የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትሯ ፕሮፌሰር ሒሩት ወልደማሪያም በዚሁ ወቅት እንደገለጹት ጀርመን የኮሮና ወረርሽኝን ለመዋጋት ላደረገችው ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።ፕሮፌሰርሂሩት፤ሳሙና የእጅ መታጠቢያ 213 ሺህ ኢንፍራሬድ ቴርሞሜትር 50 ያሕል ሰራተኞችችን ከቤታቸው ሆነው እንዲሰሩ የሚያስች ዋይፋ አፓራተስ አበርክተውልናል። እነዚህ ቁሳቁስ ለቴክኒክና ሙያ ተቋሞችና ለዩኒቨርሲቲዎች የምናሰራጫቸው ይሆናል።ብለዋልድጋፉ በትምህርት ተቋማት ወረርሽኙን ለመከላከል የሚደረገውን ጥረት እንደሚያግዝ ተገልጿል፡፡

ህገ ወጥ የጦር መሳሪያ ዝውውርን በመቆጣጠር በኩል ውጤታማ ስራ ተከናውኗል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ገለፁ::

አዲስ አበባ፣ግንቦት6፣2012 ህገ ወጥ የጦር መሳሪያ ዝውውርን በመቆጣጠር በኩል ውጤታማ ስራ ተከናውኗል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ገለፁ:: ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ባለፉት ጥቂት ወራት ህገ ወጥ የጦር መሳሪያ ዝውውርን በመቆጣጠር በኩል ውጤታማ ስራ መከናወኑን ገለጹ።ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፌስቡክ ገፃቸው ባስተላለፉት መልእክት ባለፉት ጥቂት ወራት ሕገ ወጥ የጦር መሣሪያ አዘዋዋሪዎችን ተከታትሎ በመያዝ አኩሪ ሥራ ተሠርቷል። […]

በኢትዮጵያ በ24 ሰዓታት ውስጥ በተደረገ የላቦራቶሪ መምርመራ 14 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኘባቸው

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 11፣ 2012 በኢትዮጵያ በ24 ሰዓታት ውስጥ በተደረገ የላቦራቶሪ መምርመራ 14 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኘባቸው የጤና ሚኒስቴር በመግለጫው እንዳስታወቀው በ24 ሰዓታት ውስጥ በ3 ሺህ 271 ሰዎች ላይ በተደረገ ምርመራ ነው ታማሚዎቹ የተለዩት፡፡ በቫይረሱ የተያዙት ሁሉም ኢትዮጵያዊያን ሲሆኑ እድሜያቸው ከ9 እስከ 65 ዓመት የዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ 11 ወንዶችና 3 ሴቶች መሆናቸው ታውቋል፡፡ በምርመራ […]