loading
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 6ተኛዉ አገር አቀፍ ምርጫን ለማካሄድ ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ገለፀ::

አዲስ አበባ፣ መስከረም 22፣ 2013 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 6ተኛዉ አገር አቀፍ ምርጫን ለማካሄድ ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ገለፀ::ቦርዱ አያደረገ ያለዉን ዝግጅት ለጋዜጠኞች አስጎብኝቷል፡፡ምርጫ ቦርዱ ለምርጫ ከሚያስፈልጉት ቁሳቁሶች 90 በመቶ ያህሉንም ገዝቶ ማጠናቀቁን ገልጿል፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባዘጋጀዉ ጉብኝት ለምርጫ የሚያግዙትን የድምጽ አሰጣጥ ቁሳቁስና ምዝጋበ ሂደት ምን እንደሚመስል በኢግዚቢሽን ማዕከልና በኢትዮጵያ አየር መንገድ ካርጎ ዉስጥ […]

ግብረገብነት ያለው ትውልድ ለማፍራት የስርዓተ ትምህርት ክለሳ እየተደረገ ነው::

አዲስ አበባ፣ መስከረም 25፣ 2013 ግብረገብነት ያለው ትውልድ ለማፍራት የስርዓተ ትምህርት ክለሳ እየተደረገ ነው:: ግብረገብነት ያለው በስብዕና እውቀት የተገነባ ትውልድ ለማፍራትየስርዓተ ትምህርት ክለሳ እየተደረገ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር ገለፀ ::በአጠቃላይ ትምህርት እየተካሄደ ያለውን ሪፎርምና የቀጣይ አስር ዓመት መሪ እቅድ ዙሪያ የተዘጋጀ የውይይት መድረክ በአዳማ ተካሄዷየትምህርት ሚኒስትር ዶክተር ኢንጂነር ጌታሁን መኩሪያ በመድረኩ እንደገለጹት የአጠቃላይ ትምህርት ሴክተር የተማሪዎች […]

በፓሪስ የኮሮናቫይረስ ስርጭት በድጋሚ ማገርሸቱ ተሰማ::

አዲስ አበባ፣ መስከረም 25፣ 2013 በፓሪስ የኮሮናቫይረስ ስርጭት በድጋሚ ማገርሸቱ ተሰማ::በፈረንሳይ ዋና ከተማና ፓሪስና ማርሴል የኮሮና ቫይረስ ስርጭት በድጋሚ በማገርሸቱ ምክንያት በርካታ ተቋማት ለአገልግሎት ዝግ ሆነው እንዲቆዩ መወሰኑ ተሰምቷል፡፡ በሀገሪቱ ባገረሸው የኮቪድ 19 ስርጭት ምክንያት በዋና ከተማዋ ፓሪስ የሚገኙ የምሽት መዝናኛዎችና ሬስቶራንቶች ከማክሰኞ ጀምሮ ዝግ ሆነው እንዲቆዩ የሀገሪቱ ባለስልጣናት ማዘዛቸውን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡ትላንት በወጣው የሀገሪቱ ሪፖርት […]

በሲያትል የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ አባላት የተለያዩ የሕክምና ቁሳቁስ ለጤና ሚኒስቴር አስረከቡ::

አዲስ አበባ፣ መስከረም 25፣ 2013 በሲያትል የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ አባላት የተለያዩ የሕክምና ቁሳቁስ ለጤና ሚኒስቴር አስረከቡ:: ስምንት አባላት ያሉት የልዑካን ቡድን ኮቪድ-19ን ለመከላከል የሚያስችሉ የሕክምና መሳሪያዎችና ሌሎች ቁሳቁስ ለውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ፅዮን ተክሉና ለጤና ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ ሳሕረላ አብዱላሂ አስረክበዋል::የሲያትል ኮሚኒቲ ተወካይ አቶ ፈለቀ ወልደማርያም ድጋፉ የተደረገው የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝን መከላከያና ሌሎች ቁሳቁስ እንደሚገኙበት ተናግረዋል በድጋፍ […]

በማሊ የወባ ወረርሽኝ ተቀስቅሶ በርካቶችን ለሞት መዳረጉ ተነገረ::

አዲስ አበባ፣ መስከረም 25፣ 2013 በማሊ የወባ ወረርሽኝ ተቀስቅሶ በርካቶችን ለሞት መዳረጉ ተነገረ::በሰሜናዊ ማሊ ግዛት የወባ ወረርሽኝ መቀስቀሱንና በአንድ ሳምንት ውስጥ 23 ሰዎች መሞታቸውን የጤና ባለሙያዎች ይፋ አድርገዋል የማሊ ጤና ሚኒስቴር በዚህ ሳምንት ባወጣው መግለጫ በተያዘው የፈረንጆቹ ዓመት በሰሜናዊ የሀገሪቱ ክፍል 59 ሰዎች በወረርሽኙ ምክኒያት መሞታቸውን አስታውቋልይህም የሟቾች ቁጥር ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጻር […]

ፕሮፌሰር መስፍንን የሚዘክር ፋውንዴሽን::

አዲስ አበባ፣ መስከረም 26፣ 2013 የፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም ሥራዎችን የሚዘክር ፋውንዴሽን ሊቋቋም መሆኑ ተገለፀ፡፡ የፕሮፌሰር መስፍን  የሥራ ባልደረባ የነበሩት አቶ ያሬድ ሃይለማርያም የሟቹን ሥራዎችን የሚዘከር ፋውንዴሽን እንደሚቋቋም ለኢዜአ ገልጸዋል። ፋውንዴሽኑን የማቋቋም ሀሳብ ከህልፈተ ህይወታቸው በፊት ሲታሰብ የነበረ ጉዳይ እንደነበረ ገልጸው፣ የፕሮፌሰር መስፍን ድንገተኛ ሞት ሐሳቡን ፈጥኖ ሥራ ላይ ለማዋል  አነሳሽ ሆኗል ብለዋል። ፋውንዴሽኑን በስድስት ወራት […]

ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ትምህርት ለማስጀመር መዘጋጀቱን ገለፀ::

አዲስ አበባ፣ መስከረም 26፣ 2013 ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ትምህርት ለማስጀመር መዘጋጀቱን ገለፀ:: ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል ታሳቢ ባደረግ መልኩ ትምህርት ለማስጀመር የሚያስችለውን ዝግጅት ማድረጉ ገልጿል። የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሉኡካን በዩኒቨርሲቲው የተማሪዎች ቅበላን በማስመልከት የመስክ ምልከታ አካሂዷል። በሚኒስቴሩ የከፍተኛ ትምህርት አካዳሚክ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጄኔራል ዶክተር ኤባ ሜጀና በወቅቱ እንደተናገሩት  ፤ዩኒቨርሲቲው ወረርሽኙን ለመከላከል ያከናወነው ተግባር የሚበረታታ ነው። […]

በሀገሪቱ የሳይበር ጥቃት ከተቃጣባቸው ተቋማት የሚዲያ ተቋማት በ2ኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኙ ተገለፀ፡፡

አዲስ አበባ፣ መስከረም 27፣ 2013 በሀገሪቱ የሳይበር ጥቃት ከተቃጣባቸው ተቋማት የሚዲያ ተቋማት በ2ኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኙ ተገለፀ፡፡የኢንፎርሜሽን መረብ ደሕንነት ኤጀንሲ እና የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን የመገናኛ ብዙሃን ተቋማትን ከማንኛውም የሳይበር ጥቃት ለመከላከል የሚስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡የኢንፎርሜሽን መረብ ደሕንነት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ሹመቴ ግዛው እና የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ጌታቸው ድንቁ ስምምነቱን ፈርመዋል። የመግባቢያ […]

የአልበሽር ጠበቆች ቅሬታ::

አዲስ አበባ፣ መስከረም 27፣ 2013 የአልበሽር ጠበቆች ቅሬታ::በአቃቤ ህግ ቅር የተሰኙ የአልበሽር ጠበቆች ችሎት ረግጠው ወጡ:: የቀድሞው የሱዳን ፕሬዚዳንት ኦማር ሀሰን አልበሽር ተከላካይ ጠበቆች አቃቤ ህግ አድሏዊ የሆነ ክርክር አቅርቦብናል ሲሉ ከሰዋል፡፡ በዚህም ምክንያት ከፕሬዚዳንቱ ጠበቆች መካከል የተወሰኑት የዕለቱን ክርክር በመተው ችሎቱን ረግጠው መውጣታቸው ተሰምቷል፡፡ አፍሪካ ኒውስ እንደዘገበው አልበሽር በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ሆነው ቢገኙ እስከሞት […]

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አመራሮች የምርጫ ቦርድን የምርጫ ዝግጅት ጎበኙ::

አዲስ አበባ፣ መስከረም 29፣ 2013 የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አመራሮች የምርጫ ቦርድን የምርጫ ዝግጅት ጎበኙ::የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎና የምክር ቤት አመራሮች የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የምርጫ ቅድመ ዝግጅትን እየጎበኙ ነው። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛው አገር አቀፍ ምርጫ የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ የመከላከያ መንገዶችን በመተግበር እንዲካሄድ ከጤና ሚኒስቴር የቀረበለትን ምክረ ሃሳብ በተጨባጭ በማጤን […]