loading
የአሜሪካ መንግስት ልኡካን በኢትዮጵያ ጉብኝት ለማድረግ በዛሬው እለት አዲስ አበባ ይገባሉ።

በሪፐብሊካን ኮንግረስማን ክሪስቶፈር ስሚዝ የሚመራው የልኡካን ቡድን በኢትዮጵያ እየመጡ ባሉ ለውጦች ዙሪያ ከኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አበይ አህመድ እና ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ወርቅነህ ገበየሁ ጋር ተገናኝተው እንደሚወያይም ይጠበቃል። የልኡኩ መሪ ኮንግረስማን ክርስቶፈር ስሚዝ ከአሜሪካ ድምፅ (ቪኦኤ) ራዲዮ ጋር ባደረጉት ቆይታ፥ በኢትዮጵያ በሚኖራቸው ቆይታ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ እና ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ወረቅነህ ጋር […]

የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት ለመስጠት እየሰራ ነው አለ፡፡

ተቋሙ ባለፉት አመታት ለፓርቲ የወገነ አሰራር መተግበሩና ከተሰጠው አገራዊ ተልእኮ ውጪ ዜጎችን የማፈን የማሰርና ኢሰብአዊ ምርመራ ሲያደርግ መቆየቱ ተቋሙ እንዲፈራ አድርጎት ቆይቷል ተብሏል፡፡ የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ጀነራል አደም መሀመድ ከኢቢሲ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደተናገሩት ከተቋሙ አሰራር ጋር በተያያዘ የሚነሱ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታትም ተቋሙ የተቋቋመበትን አዋጅ ማሻሻልን ጨምሮ የሪፎርም ስራዎችን እያከናወነ ነው ፡፡ በተቋማዊ የሪፎርም ስራው […]

ባለፈው ሰኔ በአሶሳ በተከሰተው የፀጥታ ችግር ጉዳት የደረሰባቸው ወገኖች ድጋፍ ለማድረግ መወሰኑን የክልሉ መንግስት አስታወቀ፡፡

ያን ግዜ በተከሰተው የፀጥታ ችግር ህይወታቸውን ላጡና ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ከ2 ሚሊዮን ብር በላይ ለድጋፍ አጽድቋል፡፡ የቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል መንግስት በግጭቱ ምክንያት ህይወታቸው ላለፈ 16 ግለሰቦች ቤተሰብ ለእያንዳንዳቸው 30 ሺ ብር፣ በግጭቱ ምክንያት ከባድ የአካል ጉዳት ለደረሰባቸው 11 ግለሰቦች ለእያንዳንዳቸው 20ሺ ብር እንዲሁም በግጭቱ ምክንያት ቀላል ጉዳት ለደረሰባቸው 78 ግለሰቦች ደግሞ ለእያንዳንዳቸው 10 ሺ ብር […]

የአሜሪካና የቻይና የንግድ ጦርነት ተባብሷል፡፡

ሲጂቲኤን እንደዘገበው ሁለቱ ሀገሮች ብድር እየተመላለሱ አንዱ በሌላው ላይ የታሪፍ ጭማሪ መቀጠሉን ተያይዘውታል፡፡ አሁን አሜሪካ በቻይና ምርቶች ላይ የ25 በመቶ የታሪፍ ጭማሪ መጣሏን ተከትሎ ቻይናም በብርሃን ፍጥነት በዋሽንግተን ምርቶች ላይ ተመሳሳይ ታሪፍ ጥላባቸዋለች፡፡ አሜሪካ የ25 በመቶ ታሪፍ የጣለችው ከቻይና ወደ ሀገሯ በሚገቡ የኤሌክትሮኒክስ፣ የፕላስቲክ፣ የባቡር መገጣጠሚያ መሳሪያዎችና የኬሚካል ውጤቶች ላይ ሲሆን ቻይና በአጸፋው በተሸከርካሪዎች፣ በኢነርጂና […]

በፍቅር እንደመር በይቅረታ እንሻገር በሚል መሪ ቃል ጳግሜ 5 ቀን የአዲሱን አመት መግቢያ በማስመልከት አዲስቷን ኢትዮጵያን ለመገንባት ቃል የመግባት ፕሮግራም በሚሊኒየም አዳራሽ ይካሄዳል፡፡

የመንግስት ኮምኒኬሽን ጉዳች ፅህፈት ቤት ሚኒስትር ድኤታ አቶ ካሣሁ ጎርፌ ዛሬ በሰጡት መግለጫ በዝግጅቱ አድስቷን ኢትዮጵያ ለመገንባት የሚያስችለንን ቃል የምንገባበት ከመሆኑም በላይ በሁለም የህብረተሰብ ከፍል እና በመላው ሀገሪቱ የመነቃቃት ስሜት በሚፈጠርበት በመደመር ስሜት በውጭ ሀገር የሚኖሩትን ጨምሮ አዲሲቷ ኢትዮጵያ በጋራ የምንገነባበት እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ በዝግጅቱ ከ 2 መቶ በላይ ኤርትራውያን ለመጋበዝ ከውጭ ጉዳይ ጋር በጋራ በመሆን […]

ቴል አቪቭ ከዋሽንግተን ሌላ ውለታ እየጠበቀች ነው፡፡

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚንስትር ቤናሚን ኔታናያሁ እራኤል ከሶሪያ በሀይል የወሰደችውን የጎላን ተራራን የባለቤትነት እውቅና እንድትሰጣት አሜሪካን አጥብቀው ጠይቀዋል፡፡ ከአሁን ቀደም እየሩሳሌም የእስራኤል ዋና ከተማ ናት የሚለውን ውሳኔ ያሳለፈው የትራምፕ አስተዳደር አሁን ደግሞ ለጎላን ተራራ ሌላ እውቅና እንዲሰጠን የምንችለውን ሁሉ እናደርጋለን ብላል ኔታናያሁ፡፡ ኔታናያሁ ይህን ያሉት የአሜሪካው የደህንነት አማካሪ ጆን ቦልተን ሀገራቸው እስካሁን የጎላን ተራራ ለእስራኤል ይገባታል […]

የአቃቂ ግድብ መሙላት አደጋ ስለሚያስከትል የማስተንፈስ ስራ አሁንም ይቀጥላል ተባለ፡፡

ይህንን ያለዉ የአዲስ አበባ ዉሃና ፍሳሽ ባለስልጣን ነዉ፡፡ በባለስልጣኑ የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች የስራ ሄደት መሪ አቶ እስጢፋኖስ ብስራት ለአርትስ ቲቪ በትላንትናው ዕለት አቃቂ አካባቢ የደረሰውን የጎርፍ አደጋ ተከትሎ በተለያዩ ማህበራዊ ድረገፆች ላይ የአቃቂ ግድብ ሞልቶ ለማስተንፈስ በተደረገ ጥረት ውስጥ ቸግሩ እንደተከሰተ እና የሚመለከተውም አካል ማስጠንቀቄያ እንዳልተሰጠ ተደርጎ ሲነገር የነበረዉ ሀሰት ነዉ ብለዋል፡፡፡ በክረምት ሁሌ የማስተንፈስ ስራ […]

የብአዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ ብአዴን ወደፊት የሚመራባቸውን የፖለቲካ መስመሮች ለመወሰን እየመከረ ነው፡፡ 

የብአዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ ይመራበት የነበረውን አብዮታዊ ዲሞክራሲ እናሻሽል ወይም አናሻሸል በሚሉ እና ሌሎች መሰረታዊ ጉዳዮች ላይ እየመከረ ነው፡፡ በዋናነትም አብዮታዊ ዴሞክራሲን እናሻሽል ወይም አናሻሸል? በሚል መሰረታዊ የማሻሻያ ጉዳዮችይወያያል፡፡ የድርጅቱ ስያሜ እና ዓርማ የአማራን ህዝብ አይወክልም በመባሉም ይመከርበታል፡፡ ድርጅቱ ባለፉት ጊዜያት ይመራባቸው የነበሩ ህጎች አንዳንዶቹ ወቅቱን ያላገናዘቡ በመሆኑ ይመከርባቸዋል፡ የብአዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ በክልሉ ካሉ አመራሮች የሰበሰባቸውን […]

ጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር አብይ አህመድ ከኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል 11 ዞኖች ከተውጣጡ የሴቶችና ወጣቶች ተወካዮች፣ ምሁራንና ከተለያዩ የአለም አገራት ከመጡ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች በክልሉ ወቅታዊና የለውጥ እንቅስቃሴዎች ላይ እየተወያዩ ነው።

  ጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር አብይ አህመድ ከኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል 11 ዞኖች ከተውጣጡ የሴቶችና ወጣቶች ተወካዮች፣ ምሁራንና ከተለያዩ የአለም አገራት ከመጡ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች በክልሉ ወቅታዊና የለውጥ እንቅስቃሴዎች ላይ እየተወያዩ ነው። ምንጭ ኢቢሲ  

በኢትዮጵያ እየተካሄደ ስላለው ለውጥ አድናቆት አለን አሉ ኮንግረስማን ክሪስ ስሚዝ፡፡

  አርትስ 18/12/2010 የአሜሪካ ኮንግረንስ አባላት ልኡካን ቡድን ከኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ ጋር በአዲስ አበባ ተወያይቷል፡፡ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በድረ ገጹ እንዳስታወቀዉ ኮንግረንስማን ክሪስ ስሚዝ አሁን እየተካሄደ ያለው ለውጥ ተጠናክሮ እንዲቀጠል ጥሪ አቅርበዋል፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚንስትሩ ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ አሜሪካ ለኢትዮጵያ ዕድገት ለምታደርገው አስተዋጽኦ አድናቆታቸውን ገልጸዋል፡፡ የአሜሪካ ኮንግረስ አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርግ ጠይቀው […]