loading
ካናዳ የሊቢያ ምርጫ ህገ መንግስቱን ተከትሎ መከናወን አለበት አለች፡፡

አናዶሉ የዜና ወኩል እንደዘገበው ሊቢያ የምታካሂደው የፓርላማና ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ህገ መንግስታዊ ድንጋጌውን ተከትሎ መከናወኑ ስላለው ጠቀሜታ ተሁለቱ ሀገሮች ስምምነት ላይ ደርሰዋል፡፡ በሊቢያ የካናዳ አምሳደር ሂላሪ ቻይልደስ አዳምስ እና የሊቢያ ፕዝዳንታዊ ምክር ቤት ሊቀ መንበር ፋይዝ አል ሳራጅ ባረጉት ምክክር ነው ስምምነት ላይ የደረሱት፡፡ አምባሳደሯ እንዳሉት ሀገራቸው በሊቢያ ዓለም አቀፍ እውቅና የተሰጠውን መንግስት ለመደገፍ ዝግጁ ነው፡፡ […]

የቀድሞ የአፋር ክልል ፕሬዝደንት የነበሩት ሱልጣን ሀንፍሬ አሊ ሚራህ አዲስ አበባ ገቡ፡፡

በሱልጣን ሐንፈሬ አሊ ሚራህ የሚመራውና በስደት በውጭ አገራት ሲኖሩ የነበሩ ልኡካን ቡድን አባላት ዛሬ አዲስ አበባ መግባቱን ኢብኮ ዘግቧል፡፡ ከአፋር ህዝብ ፓርቲ ዶ/ር ኮንቴ ሙሳ ፣ከአፋር ሰብዓዊ መብት አቶ ጋአስ አህመድ እና ከአፋር ነፃ አውጪ ግንባር አቶ ኡመር አሊሚራህ ይገኙበታል፡፡ ልኡካኑ አዲስ አበባ አለም አቀፍ ኤርፖርት ሲደርሱ የኢፌዲሪ መንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ ሚኒስትሮች፣ የአፋር ብሄራዊ […]

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሀጅ ተጓዦች ላይ የተፈጠረውን የበረራ መስተጓጎል ችግር ለመቅረፍ እየሰራ መሆኑን አስታውቋል፡፡

ከትላንትናው ዕለት ጀምሮ የሀጅ ተጓዦች በረራቸው ተሰርዞ በአየር መንገድ ውስጥ ያለ በቂ ምግብና ማረፊያ እየተጉላላን ነው ብለዋል፡ ይህን ተከትሎ አቢሲ ወደ ኢትዮጵያ አየር መንገድ ስልክ ደውሎ ስለ ሁኔታው ለማጣራት ቢሞክርም አየር መንገድ ስለ ጉዳዩ በፌስ ቡክ ገፁ ካወጣው መረጃ ተጨማሪ የሚሰጠው መረጃ እንደሌለው የህዝብ ግንኙነት ክፍል አስታውቋል፡፡ አየር መንገዱ በፌስ ቡክ ገፁ ባወጣው መግለጫ በሀጅ […]

የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴና አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አትሌት ፈይሳ ሌሊሳ ወደ ሀገሩ እንዲመለስ ጥሪ አቀረቡለት

የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴና የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በጋራ ባወጡት መግለጫ ነው አትሌት ፈይሳ ሌሊሳን ወደሀገሩ እንዲመለስ መጋበዛቸውን ያስታወቁት። በመግለጫቸውም በሪዮ ኦሎምፒክ እና በልዩ ልዩ የዓለም አትሌቲክስ መድረኮች በመሳተፍ የሀገሪቱ ሰንደቅ ዓላማ ከፍ ብሎ እንዲውለበለብ አስተዋጽኦ ያበረከተው አትሌት ፈይሳ ሌሊሳ ወደ ሀገሩ እንዲመለስ ፍላጎታቸው መሆኑን አስታውቀዋል። የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴና የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በወጣቶችና ስፖርት ሚኒስቴር አስተባባሪነት በተዘጋጁት […]

የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) ልኡካን ቡድን አዲስ አበባ ገባ።

ልዑኩ ወደ ሀገር ቤት የመጣውም በኢትዮጵያ መንግስት እና በኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) መካከል ባሳለፍነው ነሃሴ 1 2010 ዓ.ም የእርቅ ስምምነት መፈረሙን ተከትሎ ነው። ልዑኩ አዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርስም የኦህዴድ የከተማ ፖለቲካና የድርጅት ዘረፍ ሀላፊ አቶ ከፍያለው አያና እናሌሎች የኦሮሚያ ክልል ከፍተኛ ባለስልጣናት አቀባበል አድርገውለታል። የልዑካን ቡድኑን የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ስራ አስፈጻሚ […]

የኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ወርቅነህ ገበየሁ ከጅቡቲ ፕሬዝዳንት ኢስማኤል ኦማር ጊሌ ጋር በጅቡቲ ተወያዩ።

የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በድረ ገጹ እንዳስታወቀዉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶክተር ወርቅነህ ገበየሁ፥ በኢትዮጵያ እና ጅቡቲ መካከል ያለው ግንኙነት በሁኔታዎችና በአጋጣሚ የማይለወጥ ስትራቴጂካዊ ወዳጅነት ነዉ ብለዋል፡፡ ዶክተር ወርቅነህ፥ በድሬዳዋ በተፈጠረው ክስተት የጅቡቲ ዜጎች ህይወታቸውን በማጣታቸው ማዘናቸውን ገልጸዋል፡፡ የተፈጠረው ክስተት የሁለቱን ህዝቦች አጠቃላይ ግንኙነት አያሳይም ያሉት ዶክተር ወርቅነህ፥ ጥፋተኞቹ በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተደረገ በመሆኑ በሕግ ተገቢውን […]

በ2019 የታዳጊዎች አፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ እየተሳተፈ የሚገኘው የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን የጅቡቲ አቻውን በሰፊ የግብ ልዩነት አሸነፈ፡፡

በማጣሪያው የመጀመሪያ ጨዋታው የኡጋንዳ ቡድንን 1 ለ 0 ማሸነፉ የሚታወስ ሲሆን በሁለተኛ ጨዋታው ጅቡቲን 4 ለ 0 በመርታት ወደ ተከታዩ ደረጃ ለማለፍ የሚያደርገውን ጉዞ አሳምሯል፡፡ የቀይ ቀበሮዎቹን የድል ጎሎች በየነ ባንጃ፤ በረከት ካሌብ፤ ቢንያም አይተን፤ መንተስኖት እንድርያስ አስቆጥረዋል፡፡ እዚሁ ምድብ ኬንያ ደቡብ ሱዳንን 4 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡ በቀጣይ መጭው እሁድ ነሃሴ 13 በቻማዚ […]

የዓለም የጤና ድርጅት የዲሞክራቲክ ኮንጎ ጉዳይ አሳስቦኛል ብሏል፡፡

በሀገሪቱ የተፈጠረው አለመረጋጋት የኢቦላ ቫይረስን ለማጥፋት የሚደረገውን ጥረት አደጋ ላይ ጥሎታል ነው ያለው ድርጅቱ፡፡ አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ እንደዘገበው የዓለም ጤና ድርጅት ዳይሬክተር ጀነራል ዶክተር ቴዎድሮስ አድኃኖም አሁን በሀገሪቱ ያለው ሁኔታ በጣም አሳሳቢ ነው ብለዋል፡፡ ዶክተር ቴዎድሮስ የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ተፋላሚ ሀይሎች በአስቸኳይ ተኩስ አቁመው የጤና ባለሞያዎች እንደልባቸው ቫይረሱ ወደተከሰተበት አካባቢ ተንቀሳቅሰው ስራቸውን እንዲሰሩም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ […]

መቀመጫውን ደቡብ አፍሪካ ያደረገው ዘ በርንተስት የተባለዉ ፋውንዴሽን የቀድሞ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስትር ሀይለማርያም ደሳለኝን የአማካሪ ቦርድ አድርጎ መሾሙን ኦል አፍሪካን ዶት ኮም ዘግቧል፡፡

መቀመጫውን ደቡብ አፍሪካ ያደረገው ዘ በርንተስት የተባለዉ ፋውንዴሽን የቀድሞ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስትር ሀይለማርያም ደሳለኝን የአማካሪ ቦርድ አድርጎ መሾሙን ኦል አፍሪካን ዶት ኮም ዘግቧል፡፡ ፋውንዴሽኑ የአፍሪካን ኢኮኖሚ በአዲስ አስተሳሰብ እና በአዳዲስ ግኝቶች ለማጠናከር የተቋቋመ ነው፡፡

የሊቢያ ፍርድ ቤት ወንጀለኞች ናቸዉ ባላቸዉ 45 ሰዎች ላይ የሞት ቅጣት ፍርድ ወሰነ::

የሞት ፍርዱ የተላለፈባቸው ሰዎች ታጣቂዎች ሲሆኑ በፈረንጆቹ 2011 ትሪፖሊ ውስጥ የቀድሞውን የሀገሪቱ መሪ ሙአመር ጋዳፊን በተቃወሙ ሰዎች ላይ ተኩስ ከፍተው በመግደላቸዉ ነዉ፡፡ የሞት ቅጣት ከተላለፈባቸዉ ዉስጥ የሙአመር ጋዳፊ ልጅም ይገኝበታል ተብሏል፡፡ በሊቢያ ከጋዳፊ አገዛዝ መውደቅ በኋላ በርካታ ወንጀለኞች የሞት ቅጣት ቢተላለፍባቸውም በቁጥር ደረጃ ግን የአሁኑ ትልቁ ነው፡፡ የሞት ፍርድ ከተላለፈባቸዉ ሌላ ከ54 የሚበልጡት ላይ የአምስት […]