loading
ምክትል ከንቲባ ታከለ ኡማ አዲስ ካቢኔ ለምክር ቤቱ አዳዲስ የካቢኔ አባሎቻቸውን አቅርበዋል፡፡

ምክትል ከንቲባ ታከለ ኡማ አዲስ ካቢኔ ለምክር ቤቱ አዳዲስ የካቢኔ አባሎቻቸውን አቅርበዋል፡፡ ወ/ሮ አልማዝ አብርሃ የሴቶችና ህፃናት ቢሮ ሃላፊ ወ/ሮ ፍሬህይወት ተፈራ የፍትህ ቢሮ ሃላፊ አቶ ጀማሉ ጀምበር የወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ሃላፊ አቶ ሺሰማ ገ/ስላሴ ለገቢዎች ሃላፊ ዶ/ር ፍሬህይወት ገ/ህይወት ለፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ ሃላፊነት አቶ አሰፋ ዪሃንስ ለቴክኒክና ሙያ ቢሮ ሃላፊ ኢንጂነር ኤርምያስ ለኢንደስትሪ ቢሮ […]

ሰንደቅ ጋዜጣ ተዘጋ፡፡

በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ በአማርኛ ቋንቋ ታትመው ለገበያ የሚቀርቡ የግል ሳምንታዊ ጋዜጦችም “ሪፖርተር እና “አዲስ አድማስ” ብቻ ሆነዋል፡፡ ሰንደቅ ጋዜጣ የተዘጋው በየጊዜው እየናረ ከመጣው የሕትመት ዋጋ ጋር ተያይዞ ባጋጠመው ኪሳራ ምክንያት መሆኑን የሰንደቅ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ አቶ ፍሬው አበበ ለአርትስ ቲቪ ተናግረዋል፡፡ ጋዜጣው በሳውዲ አረቢያ ታስረው በሚገኙት ሼህ መሀመድ አላሙዲን ይደገፍ እንደነበር ይነገራል። ዋና አዘጋጁ ሰንደቅ […]

አንድ ሺህ አምስት መቶ የዘንድሮ ተመራቂዎች በአንድ ሰዓት ውስጥ ከቀጣሪዎች ጋር ይገናኛሉ፡፡

ይህ የሚሆነዉ በናሽናል ኬረርስ ኤክስፖ 2018 ነዉ፡፡ የትምህርት ሚኒስቴር ከኢትዮ ጆብስ ጋር በጋራ በመሆን ˝ ናሽናል ኬረርስ ኤክስፖ 2018 ˝ በሚል የዘንድሮ አመት ስራ ፈላጊ ተመራቄዎችን ከተለያዩ ድርጅቶች ጋር የሚገናኙበት መድረክ በሚሊኒየም አዘገጅቷል፡፡ የኢትዮ ጆብስ ሪጅናል ኮርዲኔተር ወ/ሮ ህሊና ለገሰ ለአርትስ ቲቪ እንደተናገሩት ለመጀመሪያ ግዜ በተዘጋጀው አውደ ርዐዩ ቁጥራቸው አንድ ሺህ አምስት መቶ የዘንድሮ ተመራቂዎች […]

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በ2010 በጀት አመት ከ89 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ አገኘሁ አለ፡፡

ገቢዉ ካለፈዉ አመት ጋር ሲነጻጸር የ1/4ኛ አድገት ማሳየቱንና፤ የተጣራ 6.8 ቢሊዮን ብር ማትረፉንም ተናግሯል፡፡ ዛሬ አየር መንገዱ የዘንድሮውን አመት እቅድ አፈጻጸም አስመልክቶ ባቀረበዉ ሪፖርት እንደጠቆመዉ በዚህ ዓመት በአፍሪካ ሀገራት የነበረዉን አለመረጋጋት፣የንግድ ጦርነት ፣የነዳጅ ዋጋ መጨመር ችግር የነበረ ሲሆን፤ከአየር መንገዱ አጠቃላይ ወጪ 40 በመቶ የሚሆነዉ ለነዳጅ ወጪ ሆኗል፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ተወልደ […]

አቡዳቢ ከኢትዮጵያ ወደ ኤርትራ የነዳጅ ማስተላለፊያ መስመር ልትዘረጋ ነው ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድና የተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች የዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር ሪም አል ሃሺሚ አዲስ አበባ ላይ ተገናኝተው በጉዳዩ ዙሪያ ተወያይተዋል። ሚድል ኢስት ሞኒተር የኢትዮጵያ የስራ ኃላፊዎችን ጠቅሶ እንደዘገበው የነዳጅ ማስተላለፊያ መስመሩ ከአዲስ አበባ አሰብ ይዘረጋል ። የጠቅላይ ሚንስትሩ የጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ፍጹም አርጋ ለሮይተርስ እንደተናገሩት ከአቡዳቢ ጋር የተደረገው ውይይት በኢንቨስትመንት፣በግብርናና በሌሎች ዘርፎች […]

የዘንድሮው የሻደይ በዓል ከነሐሴ 16 እስከ 18 በዋግኸምራ ብሔረሰብ ዞን” ሻዴይ በዓላችን ለገጽታ ግንባታችን” በሚል መሪ ቃል በድምቀት ይከበራል፡፡

የዋግኸምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ፅሕፈት ቤት ሃላፊ አቶ ሰለሞን ተክሉ ለአርትስ እንደገለጹት በዓሉ በሁሉም ወረዳዎች በጎዳና ላይ ትርኢቶች እና ባህላዊ ክዋኔዎች ይከበራል ፡፡ ከበዓሉ አከባበር ጎን ለጎን በሰቆጣ ከተማ የባህል ሲምፖዚየም የሚካሄድ ሲሆን የተለያዩ ጥናታዊ ጽሁፎች ይቀርባሉ ተብሏል፡፡ በዓሉን በዩኔስኮ ለማስመዝገብ እንቅስቃሴዎች መጀመራቸውን ኃላፊው ተናግረዋል፡፡ ጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር አብይ አህመድ እና የቀድሞው ምክትል ጠቅላይ […]

ዘንድሮ የአሸንዳ በዓል በትግራይ ክልል በድምቀት ይከበራል አለ የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ፡፡

የቢሮው ሃላፊ አቶ ዳዊት ኃይሉ ለአርትስ እንደተናገሩት በዓሉን ለማክበር አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት በመደረግ ላይ ነው ብለዋል፡፡ በዓሉ በዋነኛነት በጎዳና ላይ ትርኢቶች እና ባህላዊ ጭፈራዎች የሚደምቅ ሲሆን የፓናል ውይይት እና የፎቶ አውደርዕይ ፕሮግራሞች ጎን ለጎን እንደሚካሄዱ ኃላፊው ነግረውናል፡፡ በዓሉን ለማክበር የክልሉ ተወላጆች እንዲሁም የሀገር ውስጥ እና የውጭ ሀገራት ጎብኚዎች ወደ ክልሉ ያቀናሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጲያ ሙስሊሞች አንድነት እና ሰላም ላይ ያተኮረ የኢለሞች አንድነት እና ትብብር ጉባኤ ተካሄደ።

የአንድነት ጉባኤው የተካሄደው በኢትዮጲያ ሙስሊሞች ተቋማዊ ለውጥ የጋራ ኮሚቴ አዘጋጅነት ነው፡ሀጂ ዑመር ሰኢድ የኮሚቴው ምክትል ፀሃፊ እንደገለፁት የጉባኤው አብይ አላማ የሀገራችን ሙስሊሞችን አስተባብሮ አንድነቱን ጠብቆ የሚመራ በይዘትም በአደረጃጀትም ጠንካራ እና ሁሉን አቀፍ መሪ ድርጅት የሚቋቋምበት ህግ እና አደረጃጀት የሚያመላክት ምክረ ሀሳብ ማቅረብ እንዲሁም ወደአንድነት መምጣት ነው ብለዋል፡፡ የአንድነት እና ትብብር ኮሚቴው ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ […]

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዩስን መኖሪያ ቤታቸው ድረስ በመሄድ ጎበኙዋቸው፡፡

በጉብኝቱ ላይ የትግራይ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካዔል ተገኝተዋል፡፡ ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩም እንዳሉት አቡነ መርቆርዮስን ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር በመሆን በመጎብኘታቸው ከፍ ያለ ደስታ እንደተሰማቸው ገልጸዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጉብኝታቸው ወቅት ከአቡነ መርቆርዮስ ጋር ስለይቅርባይነትና ስለፍቅር ተወያይተዋል፡፡ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ጠቅላይ ሚኒስተሩ አቡነ መርቆርዮስን መኖሪያ ቤታቸው ድረስ ተገኝተው በመጎብኘታቸው ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡ ባለፉት 26 ዓመታት […]

የኢትዮጵያ አየር መንገድ 5 የአፍሪካ አየር መንገዶችን በሽርክና ሊያስተዳድር ነዉ፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ተወልደ ገብረማርያም እንደተናገሩት የጊኒ አየርመንገድን በ49 በመቶ፣የዛምቢያ አየር መንገድን በ45 በመቶ፣ እንደ አዉሮፓዉያን አቆጣጠር በጥቅምት የሚጀምረዉን የቻድ አየር መንገድን በ49 በመቶ ድርሻ በሽርክና ሊያስተዳድር ነዉ፡፡ የዛምቢያና የኢኳቶሪያል ጊኒ አየር መንገዶችን ደግሞ የአስተዳደራዊ ስራዉን እንዲሰራ በቀረበለት ጥያቄ መሰረት ተቀብሎ በሽርክና ለማስተዳደር መስማማቱን ነዉ አቶ ተወልደ የገለጹት፡፡