loading
የአብን ማሳሰቢያ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 21 ፣ 2013 የአገራችንን ምኅዳር ለአንድ ወገን ዘረኛና ያልተገራ ሽምጥ ግልቢያ የሚያመቻቹ ኃይሎች ከወዲሁ ከድርጊታቸው ሊቆጠቡ ይገባል ሲል አብን አሳሰበ፡፡ የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ አብን ባወጣዉ መግለጫ፤ የአማራ ሕዝብ በአገዛዙ ላይ የቀረውን ተስፋና በጎ ግምት ሁሉ አስተባብሎ መጨረሱን እና በየቦታው በአማራ ሕዝብ ላይ የሚፈፀመውን ጭፍጨፋና ፖለቲካዊ አሻጥር በማያሻማ ሁኔታ በአገር ቤትና በውጭ አገር […]

አጣየን መልሶ ለመገንባት የተጀመረ ጥረት

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 26 ፣ 2013  የወጣት ማህበራት የአጣዬ ከተማና አካባቢው ተጎጂዎችን እንዲቋቋሙ ለማገዝ ሃብት ማሰባሰብ ጀመሩ በአማራ ክልል አጣዬ ከተማንና አካባቢው ተጎጂዎችን መልሶ ለማቋቋም መንግስት የሚያደርገውን ጥረት ለማገዝ ሃብት የማሰባሰብ ሰራ መጀመሩን በክልሉ የወጣት ማህበራት አመራሮች አስታውቀዋል፡፡ የክልሉ ወጣቶች ማህበር ዋና ፀሐፊ ወጣት ከፍያለው ማለፎ ለኢዜአ እንደገለጸው፤ በአጣዬ ከተማ በደረሰው ጉዳት የክልሉን ወጣቶችን አሳዝኗል። […]

ኡስታዝ አህመዲን ጀበል ራሳቸዉን ከምርጫ አገለሉ

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 7፣ 2013  ለመጪው ሀገራዊ ምርጫ በግል ለመወዳደደር ተመዝግበው የነበሩት ኡስታዝ አህመድ ጀበል በምርጫው እንደማይሳተፉ ተናገሩ፡፡ ኡስታዝ አህመዲን ጀበል በምርጫው ለመሳተፍ እንቅስቃሴ እያደረጉ የቆዩ ቢሆንም በግል ምክንያት እራሳቸውን ማግለላቸውን በይፋዊ ፌስቡክ ገፃቸው ላይ አስፍረዋል። ኡስታዝ አህመዲን ጀበል 6ኛው ሀገራዊ ምርጫ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጅማ ከተማ ተወካይ ለመሆን እጩ ሆነው ቀርበው ነበር። […]

ምርጫ ከመደረጉ በፊት ያሉት አራት ቀናት የጥሞና ወቅት ናቸዉ ተባለ::

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 9፣ 2013   ምርጫ ከመደረጉ በፊት ያሉት አራት ቀናት የጥሞና ወቅት በመሆናቸዉ የምርጫ ውድድር እንቅስቃሴ  እንደማይደረግባቸዉ ተገለፀ የጥሞና ወቅት በቅድመ የምርጫ ዑደት ውስጥ የሚገኝ ጊዜ ሲሆን በኢትዮጵያ የምርጫ ዑደት መመሪያ መሠረት ምርጫ ከመደረጉ በፊት ያሉትን አራት ቀናት ያካትታል የሚያትት ነው፡፡ የፖለቲካ ፓርቲዎች እጩዎች እና ደጋፊዎቻቸው ቦርዱ በሚያወጣው መመሪያ መሠረት የሚየካሂዱት የምርጫ ውድድር […]

በኢትዮጵያ ላይ የተደቀነውን ብሔራዊ የደኅንነት ስጋት ለመመከት የሚጠበቅበትን ሁሉ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑን አብን ገለፀ፡፡

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 28፣ 2013 በኢትዮጵያ ላይ የተደቀነውን ብሔራዊ የደኅንነት ስጋት ለመመከት የሚጠበቅበትን ሁሉ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑን አብን ገለፀ፡፡ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ሥራ አስፈጻሚ ተወያይቶ  የደረሰባቸውን አቋሞች በተመለከተ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል፡፡ አብን በመግለጫው የመራጩ ድምፅ እንዲከበር ሰላማዊና ሕጋዊ ጥረት እንደሚያደርግና የሕዝቡን ሐቀኛ ውሳኔ ያለማወላወል እንደሚቀበል አሳውቋል፡፡ በምርጫው የመሳተፉን ውሳኔ ያደረገው በዋነኝነት ከድርጅታዊ ፋይዳዎች ይልቅ ለሀገራዊ ፖለቲካው መረጋጋትና ለዴሞክራሲያዊ ተሞክሮ ግንባታ ከሚኖረው ፋይዳ አንፃር እንደሆነም ገልጿል፡፡ የምርጫው ሂደት አጠቃላይ ድርጅታዊ ቁመናውን የሚፈትሽበት መልካም አጋጣሚ መሆኑን እንደሚገነዘብ ነው በመግለጫው ያመላከተው፡፡ በቀጣይም ከሂደቱ ያገኛቸውን ተሞክሮዎችና ትምህርቶች በማካተትና ሁለገብ የማሻሻያ እርምጃዎች በመውሰድ ለብሔራዊ ፖለቲካ የሚጠበቅበትን እንደሚወጣ ገልጿል፡፡ የውጭ ወራሪዎችና የውስጥ ቦርቧሪዎች ከተቻለ ኢትዮጵያን ለየዘውጉ አምበሎች በታትኖ ከዓለም ካርታ ለማጥፋት፤ ካልሆነ ደግሞ ውስጣዊ አንድነት የሌላት፣ ደካማና ፍላጎታቸውን ያለማንገራገር የምትቀበል አድርገው ለማሽመድመድ እየተረባረቡ ይገኛሉ ብሏል። በኢትዮጵያ ላይ የተደቀነውን የብሔራዊ የደኅንነት ስጋት ለመመከት የሚጠበቅበትን ሁሉ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑንም አብን ገልጿል፡፡ ማዕከላዊ መንግሥትና በየደረጃው ያሉ መንግሥታዊ አካላት ሀገሪቱን ከተደቀነባት የህልውና አደጋ ለመታደግ በሚደረገው ርብርብ የራሳቸውን ሚና በግልጽ ከመወሰን አንስቶ ሁሉንም ባለድርሻ አካላት ያካተተ የብሔራዊ ደኅንነት እርምጃ እንዲወስዱም አብን ጥሪ አቅርቧል፡፡ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ሀገር ወዳድ ዜጎችና በተለይም ወጣቱ የኅብረተሰብ ክፍል ሀገሪቱ ስለገጠማት የብሔራዊ የደኅንነት አደጋ ግልጽ ግንዛቤ እንዲኖራቸውና ኢትዮጵያን ለመታደግ በአንድነት እንዲሰለፉም ጠይቋል፡፡ በትግራይ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች ተመድበው ትምህርታቸውን በመከታተል ላይ የሚገኙ ተማሪዎችን የትግራይ ሕዝብ አስፈላጊውን ጥበቃና እክብካቤ እንዲያደርግ ጥሪውን አስተላልፏል፡፡

የዓለም አቀፍ ምሁራን ግልፅ ደብዳቤ ለአንቶኒዮ ጉቴሬዝ

በመላው ዓለም ከፍተኛ ተደማጭነትና ተፅዕኖ ያላቸውና አሜሪካና ካናዳን ጨምሮ በተለያዩ አህጉራት የሚገኙ ታላላቅ ዓለም አቀፍ ምሁራን እና የሲቪል ማኅበረሰብ መሪዎች፣ በትግራይ ክልል በሚደረጉ እንቅስቃሴዎች ላይ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አካላት ሲፈፀሙ የታዘቧቸውን ሚዛናዊነት የሌላቸው ተግባራት በግልፅ በመናገራቸው፤ በድርጅቱ የሥራ ዕገዳ የተጣለባቸው ሁለት የመንግሥታቱ ድርጅት የኢትዮጵያ ተጠሪዎች አስፈላጊ ከለላ እንዲደረግላቸውና ወደሥራቸው እንዲመለሱ የሚጠይቅ ግልፅ ዓለም አቀፋዊ ደብዳቤ […]

በጦርነት የወደሙ ከተሞችን መልሶ ለማቋቋም 58 ከተሞች የጥምረት ስምምነት መፈራረማቸውን የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ገለጸ።

አዲስ አበባ፣ የካቲት 15፣ 2014 በጸጥታ ችግር ጉዳት የደረሰባቸውን ከተሞች መልሶ የመገባንት ሂደት በተፋጠነ መልኩ ለማስኬድ የሚያግዝ አሰራር መዘርጋቱንም አስታውቋል። ሚኒስቴሩ የበጀት ዓመቱት የመጀመሪያ ስድስት ወራት የስራ አፈጻጸም የገመገመ ሲሆን፤ በቤቶች ግንባታ፣ በመሬት አቅርቦትና የግንባታውን ዘርፍ በማዘመን፣ ከተሞችን ለነዋሪዎች የተሻለና ምቹ በማድረግ የአሰራር ማዕቀፍ መዘርጋቱ ተገልጿል። የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ፋንታ ደጄን እንዳሉት፤ […]