loading
ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስና ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሪዮስ ቀጣይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ፓትሪያሪክ ማን ይሆናል?

ይህ ጥያቄ ከእርቁ በኋላ የሚመለስ ቢሆንም ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ግን ለቢቢሲ አማርኛዉ እንደተናገሩት ከሁለቱ ፓትርያሪኮች መካከል የስልጣን መንበሩ ላይ መቀመጥ ያለበት የሚለው ጥያቄ ማነቆ ሆኖ የቆየ ቢሆንም እርሱን አሁን መፍታት ብዙም አይገድም ብለዋል። ብፁዕ አቡነ ማቲያስ የአስተዳደሩን ስራ እየሰሩ፤ አቡነ መርቆሪዮስን ደግሞ በመንበራቸው ሆነው ከአስተዳደሩ ስራ ግን ገለል እንዲሉ ስማቸውም በቅዳሴ እየተጠራ በሲኖዶሱም እየተገኙ እንዲቀጥሉ […]

የ12ኛ ክፍል የዩኒቨርሲቲ የመግቢያ ፈተና እስከ ሐምሌ 25 ባለዉ ግዜ ዉስጥ ይፋ ይሆናል

የሐገር አቀፍ ትምህርት ፈተናዎች እና ምዘና ኤጀንሲ በስሜ በሀሰት የተከፈቱ የተለያዩ የፌስ ቡክ ፔጆች የ12ኛ ክፍል ፈተና ወጥቷል፡፡ በሚል ያስወሩት ወሬ ሀሰት ነዉ ብሏል፡፡ ኤጀንሲዉ አስከ ሀምሌ 25 ግን የፈተናዉ ዉጤት ይፋ እንደሚሆን ለአርትስ ቲቪ ተናግሯል፡፡ በኤጀንሲዉ የህዝብ ግንኙነትና ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ረዲ ሾና ለጣቢያችን ፈተናዉ ገና በእርማት ላይ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የሀገር አቀፍ ትምህርት […]

የኢንጀነር ስመኘው በቀለ የቀብር ስነ – ሥርዓትን እሁድ ሀምሌ 22 ቀን 2010 ዓ.ም ይፈጸማል

የኢንጀነር ስመኘው በቀለ የቀብር ስነ – ሥርዓትን እሁድ ሀምሌ 22 ቀን 2010 ዓ.ም ይፈጸማል ፡፡ ብሔራዊ የቀብር አስፈሚ ዐብይ ኮሚቴ ለአርትስ በላከዉ መግለጫ የቀብር ሥነ-ስርአቱ ዕሁድ ሐምሌ 22 ቀን 2010. ከቀኑ 7፡00 ሰአት በአዲስ አበባ ከተማ አራት ኪሎ በሚገኘው በቅድስት ስላሴ ካቴድራል ቤተክርስቲያን ቤተሰቦቻቸው፣ ከፍተኛ የመንግሥት አመራሮች፣ ወዳጅ ዘመዶች፣ የሥራ ባልደረቦች እና መላው ህዝብ በተገኙበት […]

ዛሬ በልደታ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የቀረቡት የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ግርማ ካሳ የአራት ቀናት ጊዜ ቀጠሮ ተጠየቀባቸው፡፡

ዛሬ በልደታ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የቀረቡት የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ግርማ ካሳ የአራት ቀናት ጊዜ ቀጠሮ ተጠየቀባቸው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድን በመደገፍ ሰኔ 16 ቀን 2010 ዓ.ም. በመስቀል አደባባይ የተደረገው ሰልፍ ላይ ከፈነዳው ቦምብ ጋር በተያያዘ በቁጥጥር ሥር የዋሉት ኮሚሽነር ግርማ ካሳ ላይ ፍ/ቤቱ የተጠየቀውን ጊዜ ቀጠሮ ተቀብሏል፡፡

የቅዱስ ሲኖዶሱ ምልዐተ ጉባዔ በዛሬዉ ዕለት በውጭ በሚገኘው ሲኖዶስ ላይ አሳልፏቸዉ የነበሩ ውግዘቶችን እንደሚያነሳ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽህፈት ቤት አስታወቀ።

የቅዱስ ሲኖዶሱ ምልዐተ ጉባዔ በዛሬዉ ዕለት በውጭ በሚገኘው ሲኖዶስ ላይ አሳልፏቸዉ የነበሩ ውግዘቶችን እንደሚያነሳ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽህፈት ቤት አስታወቀ። ፅህፈት ቤቱ በሰጠው መግለጫ ሀገር ውስጥ የሚገኘው ቅዱስ ሲኖዶስ በ1984፣ 1985 እና በ1999 ዓመተ ምህረቶች አሜሪካ በሚገኘው ሲኖዶስ ላይ አሳልፏቸው የነበሩ ውግዘቶችን በቅዱስ ሲኖዶሱ ምልዐተ ጉባዔ ዛሬ እንደሚያነሳ ተናግሯል። በመግለጫው፥ በመጪው ረቡዕ ወደ ሀገር ቤት […]

በፒያሳ የሚገኘዉ የዳግማዊ አፄ ምኒሊክ ሀውልት እድሳት ተጠናቀቀ::

ለስድስት ወራት በእድሳት ምክንያት ተሸፍኖ የቆየዉ ሀዉልትም በሚቀጥለዉ ሳምንት ለህዝብ ይፋ ይሆናል ተብሏል፡፡ የአዲስ አበባ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ የህዝብ ግኑኝነት ዳይሬክተር አቶ ወርቁ መንገሻ ለአርትስ ቲቪ እንደተናገሩት የቅርስ እድሳቱ ከሴባስቶፖል መድፍ ጋር 5 ሚሊዮን ብር ፈጅቷል ፡፡ ዳይሬክተሩ ለሃውልቱ እድሳት የተያዘለት የዘጠኝ ወር ግዜ ቢሆንም ቀድሞ በስድስት ወር ጊዜ ዉስጥ እድሳቱ እንደተጠናቀቀ ተናግረዋል፡፡ እድሳቱ በአዲስ […]

የአራት ማረሚያ ቤቶች አስተዳዳሪዎች ከሃላፊነታቸው ተነሱ፡፡

ከሃላፊነታቸው የተነሱት የቂሊንጦ ፤ የቃሊቲ፤ የሸዋ ሮቢት እና የድሬዳዋ ማረሚያቤቶች አስተዳዳሪዎች መሆናቸዉን አርትስ ቲቪ ለማወቅ ችሏል፡፡ የፌደራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ረዳት የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ አዲሱ ጴጥሮስ ለ አርትስ እንደለፁት፤ በቅርቡ ታራሚዎች በተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ከፍተኛ የሠብዓዊ መብት ጥሠት እንደሚፈፀምባቸው በመናገራቸዉ እና ማረሚያ ቤቱም አስተዳዳሪዎቹ ጋር ችግር እንዳለ በማረጋገጡ ከሃላፊነታቸው እንዲነሱ ተደርጓል፡፡ የቃሊቲ ከፍተኛ ጥበቃ […]

ሐምሌ 28 በሚሌኒየም አዳራሽ የቤተክርስትያን አንድ መሆንን አስመልክቶ ልዩ ጉባዔ ይካሄዳል፡፡

ጉባዔዉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን አራተኛ ፓትሪያሪክ የሆኑት የብፁዕ አቡነ መርቆሪዎስ አቀባበል አንዱ አካል ነዉ ተብሏል፡፡ የጠቅላይ ቤተክህነት ስራ አስኪያጅ አቡነ ዲዮስቆሮስ ዛሬ በሰጡት መግለጫ በሚሊኒየም አዳራሽ ሀምሌ 28 ቀን 2010ዓ.ም የሚደረገዉ ጉባዔ የቤተክርስቲያን ልደት በመሆኑ ታላላቅ የሀይማኖት አባቶች፤ ህዝበ ክርስትያኑ እና ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድን ጨምሮ አምባሳደሮችና የመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት ይገኛሉ ብለዋል፡፡ በጉባኤዉ […]

ጎንደርን ፍለጋ የተሰኘ መጽሀፍ ተመረቀ፡፡

በጋዜጠኛ ሄኖክ ስዩም የተጻፈዉ ጎንደርን ፍለጋ የጉዞ ማስታወሻ ትላንት ሲመረቅ በክብር እንግድነት የተገኙት የኢትዮጵያ የቱሪዝም ድርጅት ምክትል ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ሰርፀፍሬ ስብሀት እንደተናገሩት ጋዜጠኛ ሄኖክ የጻፈዉ መጽሀፍ ባህልን ታሪክንና ቱሪዝምን የያዘ ነዉ፤ልንጠቀምብት ይገባል ብለዋል፡፡ ጎንደርን ፍለጋ መጽሀፍ ጋዜጠኛዉ በተለያየ አካባቢዎች ባደረጋቸዉ ጉዞዎች የሰማቸዉን ያያቸዉን ታሪኮች አጣርቶ ያስቀመጠበት ነዉ፡፡ በመጽሀፉ ዉስጥ ጎንደርን ፍለጋ በደጃዝማች አያሌዉ […]