loading
ኔይማር የብረዚል አምበልነቱን በአልቬስ ተቀምቷል::

የ27 ዓመቱ ብራዚላዊ ኮከብ ኔይማር ዳ ሲልቫ ከስምንት ወራት በፊት የተረከበውን የብራዚል ብሔራዊ ቡድን የአምበልነት ሚና ተነጥቆ ለቅርብ ጓደኛው ዳኒ አልቬስ መስጠቱ ታውቋል፡፡ የብሔራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ቲቴ ይሄንን ውሳኔ ያሳለፉት ተጫዋቹ እያሳየ ባለው ስነ ምግባር ጉድለቶች እንደሆነ ተጠቁሟል፡፡ ኔይማር ከቡድን አጋሮቹ ጋር ስምምነት እንደሌለውም ይነገራል፡፡ በዚህም የፓሪስ ሴንት ዤርማ የቡድን አጋሩ አልቬስ ብራዚል ከኳታር እና […]

በአፍሪካ ዋንጫ አልጀሪያ ወደ ጥሎ ማለፉ ስታልፍ፤ ኬንያ የመጀመሪያ ጨዋታውን አሸንፋለች፡፡

በአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ሁለተኛ ግጥሚያዎች እየተከናወኑ ሲሆን ምድብ B ላይ ትናንት በውድድሩ ለመጀመሪያ ጊዜ እየተካፈለች የምትገኘው ማዳጋስካር አሌክሳንድሪያ ላይ ቡሩንዲን 1 ለ 0 በመርታት ወደ ቀጣዩ ዙር የማለፍ ዕድሏን አስፍታለች፡፡ የማርኮ ኢላይማ ሃሪትራ ብቸኛ ጎል ደግሞ በምድቡ አራት ነጥብ ላይ እንድትደርስ አግዟል፡፡ በቀጣይ ከምድቡ ማለፏን ለማረጋገጥ አስቀድማ ጥሎ ማለፉን ከተቀላቀለችው ናይጀሪያ ጋር ብርቱ ፉክክር ይኖራቸዋል፡፡ […]