loading
የፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውርን በመከላከል ሂደት ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ ገለፀ::

አዲስ አበባ፣ መስከረም 15፣ 2013 የፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውርን በመከላከል ሂደት ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ ገለፀ:: ጠቅላይ አቃቤ ህግ በ2013 በጀት ዓመት ለማከናወን ባቀዳቸው ተግባራትና በአስር አመት መሪ እቅዱ ላይ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር መክሯል። በመድረኩም የህግ አወጣጥና አተገባበር፣ የሰብአዊ መብትና ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውር ጉዳዮችን በተመለከተ ውይይት ተደርጓል። በጠቅላይ አቃቤ ህግ […]

አርቲስት አልማዝ ኃይሌ (ማሚ) ከዚህ አለም በሞት ተለየች።

አዲስ አበባ፣ መስከረም 15፣ 2013 አርቲስት አልማዝ ኃይሌ (ማሚ) ከዚህ አለም በሞት ተለየች። በበርካታ የትያትርና ፊልም ስራዎች የምትታወቀው አርቲስት አልማዝ ኃይሌ (ማሚ) ከዚህ አለም በሞት ተለየች።ለሳምንታት በህመም ላይ የነበረችው አርቲስቷ ዛሬ ማለዳ ነው ማረፏ የተሰማው።የአርቲስቷ ስርዓተ ቀብር ነገ በመንበረ ፀባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ይፈፀማል።

የሱዳን ናሽናል ኡማ ፓርቲ የአረብ እስራኤል ዲፕሎማሲ ሰላምን ለማምጣት አስተዋፅዖ የለውም ሲል አጣጠለ::

አዲስ አበባ፣ መስከረም 18፣ 2013 የሱዳን ናሽናል ኡማ ፓርቲ የአረብ እስራኤል ዲፕሎማሲ ሰላምን ለማምጣት አስተዋፅዖ የለውም ሲል አጣጠለ:: የፓርቲው መሪ የቀድሞው የሱዳኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ሳዲቅ አልመሃዲ እስራኤል ከአረቡ ዓለም ጋር የጀመረችውን የዲፕሎማሲ ግንኙነት መደገፍ እጅ እንደመስጠት ይቆጠራል ብለዋል፡፡ ኖርማላይዜሽን በሚል አዲስ ታክቲክ እስራኤል የጀመረችው የዲፕሎማሲ ግንኙነት ሰላምን ከማምጣት ይልቅ ሌላ የፖለቲካ አጀንዳ መስፈፀሚያ ነው ሲሉም […]

የማሊ ወታደራዊ የሽግግር መንግስት ፕሬዚዳንት አዲስ ጠቅላይ ሚኒስትር ሾሙ::

አዲስ አበባ፣ መስከረም 18፣ 2013 የማሊ ወታደራዊ የሽግግር መንግስት ፕሬዚዳንት አዲስ ጠቅላይ ሚኒስትር ሾሙ:: የሽግግር ወቅቱ ፕሬዚዳንቱ ባህ ንዳዉ የሀገሪቱ ጠቅላይሚኒስትር አድርገው የሾሙት የቀድሞውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሞክታር ኡኔን ነው፡፡ የማሊ የሽግግር መንግስት ሲቪል ጠቅላይ ሚኒስትር መሾሙ ከምእራብ አፍሪካ ኢኮኖሚ ማህበረሰብ የተጣለበትን ማዕቀብ ለማላላት ሁነኛ መንገድ ሊሆንለት ይችላል ተብሏል፡፡ አልጀዚራ እንደዘገበው የማሊ ጄኔራሎች ፕሬዚዳንት ቡበከር […]

በዞኑ 285 የዳስ መማሪያ ክፍሎች በህንጻ ግንባታ ተለወጡ::

አዲስ አበባ፣ መስከረም 18፣ 2013 በዞኑ 285 የዳስ መማሪያ ክፍሎች በህንጻ ግንባታ ተለወጡ::በዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን 285 የዳስ መማሪያ ክፍሎች ወደ ህንጻ ግንባታ መለወጣቸውን የዞኑ ትምህርት መምሪያ አስታወቀ።በሰሜን ወሎም ከ56 ሚሊዮን ብር ባላይ ወጭ የተገነቡ ትምህርተ ቤቶች ለአገልግሎት መዘጋጀታቸው ተነግሯል ። የዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ትምህርት መምሪያ የግንባታ መሃንዲስ አቶ አራጋው አዲሱ ለኢዜአ […]

በፀጥታ ችግር ሳቢያ ንብረታቸውን ላጡ አሰሪዎች የድጋፍ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር ይፋ ሆነ::

አዲስ አበባ፣ መስከረም 19፣ 2013  በፀጥታ ችግር ሳቢያ ንብረታቸውን ላጡ አሰሪዎች የድጋፍ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር ይፋ ሆነ :: የድጋፍ ማሰባሰቢያው ከአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ ጋር ተያይዞ በተነሳው ሁከት ለዓመታት ሰርተው ያፈሩት ሀብትና ንብረታቸው የወደመባቸውን አሰሪዎች መልሶ ሟቋቋሚያ ነው ተብሏል።”አሰሪው ለአሰሪው” የተሰኘው ይህ መርሃ ግብር የአገሪቷን የኢኮኖሚ እድገት ለማስቀጠል፣ ማኅበራዊ መረጋጋት ለመፍጠርና ስራ ፈጣሪዎችን መልሶ ለማቋቋም […]

ሀብታቸውን ያላስመዘገቡ የክፍለ ከተማና የወረዳ አመራሮች በገንዘብ ቅጣት ሀብታቸውን እንዲያስመዘግቡ ሊደረግ ነው::

አዲስ አበባ፣ መስከረም 18፣ 2013 ሀብታቸውን ያላስመዘገቡ የክፍለ ከተማና የወረዳ አመራሮች በገንዘብ ቅጣት ሀብታቸውን እንዲያስመዘግቡ ሊደረግ ነው:: ሀብታቸውን ያላስመዘገቡ የክፍለ ከተማና የወረዳ አመራሮች በገንዘብ ቅጣት ሀብታቸውን እንዲያስመዘግቡ ሊደረግ መሆኑን የፌደራል የሥነ-ምግባርና ጸረ-ሙስና ኮሚሽን አስታወቀ።የፌደራል የሥነ ምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን በአዲስ አበባ ከአሥሩም ክፍለ ከተሞች ከተውጣጡ አመራሮች ጋር በሀብት ምዝገባ ዙሪያ ውይይት አካሂዷል።በዚህም በተቀመጠው መደበኛ የሀብት ማስመዝገቢያ […]

የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማይክ ፖምፒዮ በሶስት የምስራቅ እስያ ሀገራት ጉብኝት ሊያደርጉ ነው::

አዲስ አበባ፣ መስከረም 20፣ 2013 የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማይክ ፖምፒዮ በሶስት የምስራቅ እስያ ሀገራት ጉብኝት ሊያደርጉ ነው:: ፖምፒዮ ከመጭው ኦክቶበር 4 ጀምሮ ለጉብኝት የመረጧቸው ሀገራት ጃፓን ደቡብ ኮሪያ እና ሞንጎሊያ ናቸው፡፡ በነዚህ ሀገራት ጉብኝታቸውም በዋናነት የሰሜን ኮሪያና የቻይናን ጉዳይ አንስተው ከሀገራቱ ጋር ይመክራሉ ነው የተባለው፡፡ ፖምፒዮ ኦክቶበር 6 ላይ አሜሪካ፣ ጃፓን፣ አውስትራሊያ እና ህንድ […]

የወንጀል ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር የሚውሉት ድርጊታቸው ተጣርቶ መሆኑን የፌዴራል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ አስታወቀ፡፡

አዲስ አበባ፣ መስከረም 21፣ 2013 የወንጀል ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር የሚውሉት ድርጊታቸው ተጣርቶ መሆኑን የፌዴራል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ አስታወቀ፡፡በሀገሪቱ ከ2013 እስከ 2022 ለአስር ዓመታት የሚተገበረውን የተቋሙን ስትራቴጂክ እቅድ በተመለከተ ከክልል የጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ተቋማት ጋር ውይይት ተደርጓል። የፌዴራል ምክትል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ አቶ ገለታ ስዩም፤ ኢትዮጵያ በ2022 ዓ.ም የአፍሪካ የፍትህ ተቋማት ተምሳሌት እንዲትሆን ለማስቻል እየተሰራ መሆኑን […]

የተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች ወደ ጨረቃ ጉዞ በማድረግ የመጀመሪያዋ የአረብ ሀገር ልትሆን ተዘጋጅታለች ተባለ::

አዲስ አበባ፣ መስከረም 21፣ 2013  የተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች ወደ ጨረቃ ጉዞ በማድረግ የመጀመሪያዋ የአረብ ሀገር ልትሆን ተዘጋጅታለች ተባለ::ጠቅላይ ሚስትርና የአቡዳቢ አስተዳዳሪ የሆኑት ሼክ ሞሃመድ ቢን ራሽድ አል መክቱም በቱይተር ገፃቸው ላይ ባሰፈሩት ፅሁፍ ሀገራቸው የጠፈር መንኮራኩር ወደ ጨረቃ ለመላክ መዘጋጀቷን ይፋ አድርገዋል፡፡ አቡዳቢ በቅርቡ ወደ ማርስ ሳተላይት ያመጠቀች ሲሆን እንደ አውሮፓዊያኑ አቆጣጠር በ2024 መንኮራኩር ጨረቃ […]