loading
አዲስ ይፋ የሆነው የትምህርት ፍኖተ-ካርታ ትምህርት ሚኒስቴርን ሦስት ቦታ የሚያደራጅ ነው::

አዲስ ይፋ የሆነው የትምህርትና ስልጠና ፍኖተ-ካርታ ትምህርት ሚኒስቴርን በሦስት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች የሚያደራጅ መሆኑ ተጠቆመ። በትምህርት ዘርፍ አስተዳደር ላይ ማሻሻያ ያቀረቡት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር ጄይሉ ዑመር እንዳሉት ፍኖተ-ካርታው ብዙ መዋቅራዊ ለውጦችን የያዘ በመሆኑ ትምህርት ሚኒስቴር በሦስት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች እንዲደራጅ የሚያደርግ ነው። በአዲስ መልክ የሚቋቋሙት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች የከፍተኛ ትምህርትና ስልጠና […]

ኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ እቃዎችን ማምረት ካልጀመረች የውጭ ምንዛሬ እጥረቷን ልትፈታ አትችልም ተባለ፡፡

ኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ እቃዎችን ማምረት ካልጀመረች የውጭ ምንዛሬ እጥረቷን ልትፈታ አትችልም ተባለ፡፡ የዉጭ ምንዛሪ እጥረቷን ለመፍታት ድሮን ቴክኖሎጂ፣ አውቶሞቲቭ ኢንደስትሪ እና የህክምና እቃዎች ማምረት ይኖርባታልም ተብሏል፡፡ ይህ የተባለዉ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶክተር ኢንጂነር ጌታሁን መኩሪያ በኢትዮጵያ የታንዛኒያ አንምባሳደር ከሆኑት ቼንግሬ ሚካማን ጋር በምስራቅ አፍሪካ የቴክኖሎጂ ማበልፀጊያና ማምረቻ ለማቋቋም በሚቻልበት ሁኔታ ላይ በመከሩበት ወቅት ነዉ። ሳይንስና […]

የኒውዮርክ ፍርድ ቤት የቀድሞውን የትራምፕን ጠበቃ ጥፋተኛ ብሏቸዋል፡፡

የቀድሞው የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጠበቃ የነበሩት ሚካኤል ኮሆን ጥፋተኛ የተባሉት በ2016ቱ ምርጫ ለቅስቀሳ ከተመደበው ገንዘብ ህጉ ከሚፈቅደው ውጭ ክፍያ እንዲፈጸም አድርገዋል ተብለው ነው፡፡ ኮሆን በበኩላቸው ድርጊቱን መፈጸማቸውን አምነው ነገር ግን ይህን ያደረኩት ፕሬዝዳንቱ አዘውኝ ነው ብለዋል፡፡ ቢቢሲ እንደዘገበው የሚካኤል ኮሆን ጠበቃ ይህ ክፍያ ደንበኛየን ኮሆንን ወንወጀለኛ ካስባለ ለምን ፕሬዝዳንት ትራምፕን አያስጠይቅም ሲሉ ፍርድ ቤቱን ጠይቀዋል፡፡ […]

በአዲስ አበባ ለሚገኙ የጎዳና ተዳዳሪዎች ዛሬ ነፃ የህክምና አገልግሎት ይሰጣል።

የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ከዘመን እና ሞጋቾች ድራማ ጋር በመሆን ፥ ዛሬ ከቀኑ 8 ሰዓት እስከ ሌሊቱ 6 ሰዓት ድረስ በመዲናዋ ጎዳና ላይ የሚገኙ ሰዎች የህክምና አገልግሎት እንዲያገኙ ያደርጋሉ። የበጎ ፈቃድ አገልግሎቱ ወር በገባ በ16ኛው ቀን በቀጣይነት እንደሚሰጥ እና ወደ ሌሎች ከተሞችም ለማስፋት መታቀዱን የዘመን ድራማ ደራሲ አቶ መስፍን ጌታቸው ተናግረዋል። ሰኔ 16 ቀን በአዲስ አበባ […]

በአዲስ አበባ ከአዲስ አመት በፊት በክፍለከተማና በወረዳ አመራሮች ላይ ለዉጥ ይደረጋል ተባለ፡፡ 

በዚህ ሳምንትም በክፍለከተማ ደረጃ ያሉ ዋና ዋና አመራሮች እንደ አዲስ እንደሚዋቀሩ የአዲስ አበባ ከንቲባ ፅህፈት ቤት በድህረ ገፁ አስታዉቋል፡፡ የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ በወቅታዊ የከተማዋ ጉዳዮች ላይ በሰጡት መግለጫ የተጀመረውን ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የማድረግ እና አሁን እየታየ ያለውን ሀገራዊ ተስፋ ለማደናቀፍ እንዲሁም የመዲናችንን ሰላም ለማደፍረስ ሙከራዎች እየተደረጉ መሆኑን የሚያሳዩ ምልክቶች እየታዩ በመሆኑ ህብረተሰቡ […]

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ደቡብ አፍሪካን ሊጎበኙ ነው፡፡

ኢ.ቢ.ሲ በድረገፁ እንዳስነበበው የቀድሞ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ከኤስ .ኤ.ቢ.ሲ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደተናገሩት ዶክተር አብይ አህመድ ከቀጠናው ሀገራት ውጭ በሌሎች የአፍሪካ ሀገራት የሚያደርጉትን ጉብኝት የመጀመሪያው በደቡብ አፍሪካ እንዲሆን ፍላጎት አላቸው፡፡ አቶ ኃይለማርያም ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ የተላከ መልዕክት ለደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ሰርል ራማ ፖሳ አድርሰዋል፡፡ በፀረ አፓርታይድም ይሁን በነጻነት ትግል ወቅት […]

ጋዜጠኞችን የደበደቡ የዩጋንዳ ወታደሮች የእስር ትእዛዝ ወጣባቸው፡፡

የሀገሪቱ ወታደራዊ አዛዥ ጄኔራል ዴቪድ ሙሁዚ ጸጥታ የማስከበር ስራን ሽፋን አድርገው ጋዜጠኞችን በጭካኔ የደበደቡ ወታደሮች ላይ ከባድ ቅጣት እንዲተላለፍባቸው ጠበቅ ያለ ትእዛዝ አስተላልፈዋል፡፡ የኬንያው ደይሊ ኔሽን ጋዜጣ እንደዘገበው ጋዜጠኞቹ ባለፈው ሰኞ በዩጋንዳ ፖለቲከኞች ይፈቱ የሚል አመጽ ባሰነሱ ሰልፈኞች ላይ የጸጥታ ሀይሎች የሚወስዱትን ርምጃ ሲዘግቡ ነው ድብደባው የደረሰባቸው፡፡ የዩጋንዳ መከላከያ ተቋም ይህን ትእዛዝ ያስተላለፈው በሀገር ውስጥና […]

በመሬት፣ በቀበሌ ቤቶች፣ በጋራ መኖሪያ ቤቶች እና በህንፃዎች ላይ የኦዲት ሥራ በመስራት ላይ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንደገለፁት በከተማ አስተዳደሩ እስካሁን የነበሩ ተግባራትን ቆም ብሎ በማየት ሀገራዊ ለዉጡን ለማስቀጠል በመሬት፣ በቀበሌ ቤቶች፣ በጋራ መኖሪያ ቤቶች እና በህንፃዎች ላይ የኦዲት ሥራ እየተሰራ ነዉ፡፡ ምክትል ከንቲባዋ ˝የአዲስ ተስፋ ቀመር˝ በሚል መሪ ቃል አዲሱን ዓመት ለማክበር ጥላቻን በመቀነስ (-)፣ ያለንን በማካፈል (÷)፣ […]

ኢትዮ ቴሌኮም የታሪፍ ቅናሽ አደረገ፡፡ 

በዚህም መሰረት የስልክ ኢንተርኔት አገልግሎት ላይ የ43 ከመቶ፣ የብሮድባንድ ኢንተርኔት ላይ የ54 ከመቶ፣ የስልክ ድምፅ ላይ የ40 ከመቶ እንዲሁም የሞባይል የፅሁፍ መልዕክት (SMS) ላይ የ43 ከመቶ ቅናሽ ማድረጉን ሰምተናል፡፡ መረጃውን ሸገር የሰማሁት ከኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ወይዘሪት ፍሬህይወት ታምሩ ነው ብሎ በድረ ገፁ አስነብቧል።