loading
በአንድ ወር ውስጥ ከ10 ሺህ በላይ ህግ እና ደንብ የተላለፉ አሽከርካሪዎች ተቀጡ::

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 3፣ 2013 በአንድ ወር ውስጥ ከ10 ሺህ በላይ ህግ እና ደንብ የተላለፉ አሽከርካሪዎች ተቀጡ:: ባሳለፍነው መስከረም ወር ብቻ ከ10 ሺህ በላይ የትራፊክ ህግ እና ደንብ የተላለፉ አሽከርካሪዎችን መቅጣቱን የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ኤጀንሲ አስታውቋከል፡፡ ኤጀንሲው በመስከረም ወር ብቻ የትራፊክ ህግ እና ደንብን ለማስከበር ባደረኩት የቁጥጥር 10 ሺህ 711 አሽከርካሪዎች የትራፊክ ደንብ ሲተላላፉ […]

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሊቢያ ተቀናቃኝ ሀይሎች ቅድሚያ ለሀገር ሰጥተው እንዲስማሙ ጠየቀ::

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 3፣ 2013 የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሊቢያ ተቀናቃኝ ሀይሎች ቅድሚያ ለሀገር ሰጥተው እንዲስማሙ ጠየቀ:: ድርጅቱ በሁለት ጎራ ተከፍለው ጦርነት ውስጥ የገቡት ወገኖች ከራሳቸው ይልቅ ቅድሚያ ለሀገራቸውና ለህዝቡ በመስጠት እርቀ ሰላም እንዲያወርዱ ነው ያሳሰበው፡፡ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሊቢያ ተጠባባቂ ልዩ ልኡክ ስቴፋኒ ዊሊያምስ በድርድሩ ወቅት ከራስ የፖለቲካ አከንዳ ይልቅ የሀገሩን ጉዳይ የሚያስቀድም ተወያይ እንጠብቃለን […]

የጊኒ ተቃዋሚዎች መንግስት በአባሎቻቸው ላይ የወሰደውን እርምጃ አወገዙ::

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 3፣ 2013 የጊኒ ተቃዋሚዎች መንግስት በአባሎቻቸው ላይ የወሰደውን እርምጃ አወገዙ:: ጊኒ ከአምስት ቀናት በኋላ በምታካሂደው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ፕሬዚዳንት አልፋ ኮንዴ ለሶስተኛ ጊዜ እወዳዳራለሁ በማለታቸው ምክንያት ከባድ ተቃውሞ ከተቀሰቀሰ ሰነባብቷል፡፡ በሀገሪቱ የሚነቀሳቀሱት ተቃዋሚዎች እንደሚሉት መንግስት የተነሳበትን ተቃውሞ ለማስቆም በወሰደው የሃይል እርምጃ ከ90 በላይ ሰዎች ተገድለዋል፡፡ የጊኒ የደህንነት ሚኒስትር አልበርት ዳማንታንግ ካማራ ግን በተቃዋሚዎቹ […]

ዓለም ባንክ ለታዳጊ ሀገራት የኮቪድ 19 ክትባት ግዢ የሚውል 12 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር ድጋፍ አጸደቀ::

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 4፣ 2013 ዓለም ባንክ ለታዳጊ ሀገራት የኮቪድ 19 ክትባት ግዢ የሚውል 12 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር ድጋፍ አጸደቀ::የባንኩ ዳሬክተሮች ቦርድ ይፋ ባደረገው መሰረት ለታዳጊ ሀገራት የኮቪድ 19 ክትባት ግዢና ለዜጎቻቸው ምርመራና እንክብካቤ የሚውል 12 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር የገንዘብ ድጋፍ አጽድቋል የገንዘብ ድጋፉ ለአንድ ቢሊዮን ሰዎች ክትባት ማዳረስ የሚያስችል ሲሆን የዓለም ባንክ እስከ ፈረንጆቹ […]

የመቀሌ ዩኒቨርስቲ በአትሌቲክስና በብስክሌት ስፖርቶች በዓለም አቀፍ ውድድር ተሳትፈው አንፀባራቂ ድል ላስመዘገቡ ሁለት ሴት ስፖርተኞች የማበረታቻ ሽልማት ትናንት አበረከተ ።

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 4፣ 2013 የመቀሌ ዩኒቨርስቲ በአትሌቲክስና በብስክሌት ስፖርቶች በዓለም አቀፍ ውድድር ተሳትፈው አንፀባራቂ ድል ላስመዘገቡ ሁለት ሴት ስፖርተኞች የማበረታቻ ሽልማት ትናንት አበረከተ ።ዩኒቨርሲቲው ለሴት ስፖርተኞቹ የእውቅና ምስክር ወረቀትና የአንገት ሀብል ሽልማት አበርክቶላቸዋል። ዩኒቨርሲቲው ሽልማት ካበረከተላቸው ሴት ስፖርተኞች መካከል በቅርቡ በስፔን ቫለንሽያ ከተማ በተካሔደው የአትሌቲክስ ውድድር በ5 ሺህ ሜትር ሩጫ የአለም ክብረ ወሰን የሰበረችው […]

የሱዳኑ ጠቅላይ ሚኒስትር የከሰላውን አስተዳዳሪ ከስልጣናቸው አነሱ::

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 4፣ 2013 የሱዳኑ ጠቅላይ ሚኒስትር የከሰላውን አስተዳዳሪ ከስልጣናቸው አነሱ:: ጠቅላይ ሚንስትር አብደላ ሀምዶክ ባለፈው ሰኔ ወር የከሰላ ግዛት አስተዳዳሪ አድርገው ሾሟቸውን ሳልህ አማርን ከስልጣናቸው ያወረዷቸው በአካባቢው ከተነሳው የጎሳ ግጭት ጋር በተያያዘ ምክንያት ነው  ተብሏል፡፡ አማር ለግዛቲቱ የመጀመሪያው የሲቪል አስተዳዳሪ ሆነው ከተሸሙ ጀምሮ ቤጃ ከተባሉት ጎሳዎች ከፍተኛ ተቃውሞ የገጠማቸው ሲሆን ወደ ግዛቲቱ እንዳይገቡ […]

ዶክተር አረጋዊ በርሄ የህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ብሔራዊ ምክር ቤት ጽህፈት ቤት ዋና ዳይሬክተር ሆኑ::

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 5፣ 2013 ዶክተር አረጋዊ በርሄ የህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ብሔራዊ ምክር ቤት ጽህፈት ቤት ዋና ዳይሬክተር ሆኑ::ዶክተር አረጋዊ በርሄ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ህዝባዊ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ብሔራዊ ምክር ቤት ጽህፈት ቤት ዋና ዳይሬክተር ሆኑ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በዛሬው ዕለት ዶክተር አረጋዊ በርሔን የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ሕዝባዊ ተሳትፎ አስተባባሪ ብሔራዊ ምክር […]

ዩጋንዳውዊ አርቲስት እና ፖለቲከኛ ሮበርት ኪያጉላኒ ዳግም እስር ቤት ገባ::

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 5፣ 2013 ዩጋንዳውዊ አርቲስት እና ፖለቲከኛ ሮበርት ኪያጉላኒ ዳግም እስር ቤት ገባ::በቅፅል ስሙ ቦቢ ዋይን እየተባለ የሚጠራው ዩጋንዳዊው የፖፕ ሙዚቃ አቀንቃኝና ተቃዋሚ ፖለቲከኛ ከአሁን በፊትም መንግስትን ተቸህ ተብሎ በተደጋጋሚ ለእስርተዳርጎ ያውቃል፡፡ ፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒን አጥብቆ በመተቸት የሚታወቀው ቦቢ ዋይን አዲስ ባቋቋመው ፓርቲ ፅህፈት ቤቱ በፖሊስ ተይዞ መወሰዱን ጠበቃው ተናግረዋል፡፡ ጠበቃው አክለው እንዳሉት […]

የፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ልጅ ባሮን ትራምፕ በኮሮናቫይረስ መያዙ ተሰማ::

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 5፣ 2013 የፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ልጅ ባሮን ትራምፕ በኮሮናቫይረስ መያዙ ተሰማ:: ከሁለት ሳምንት በፊት ከባለቤታቸው ጋር ጋር በቫይረሱ ተይዘው በለይቶ ማቆያ የሰነበቱት ቀዳማዊት እመቤት ሜላኒያ ትራምፕ የልጃቸውን በበሽታው መያዝ ይፋ አድርገዋል፡፡ የ14 ዓመቱ ባሮን ትራምፕ ተመርምሮ የመጀመሪያ ውጤቱ ኔጌቲቨ እንደነበር የገለፁት ቀዳማዊት እመቤቷ እኔና ባለቤቴ በበሽታው መያዛችንን ሳውቅ ስለልጃችን አብዝቸ ስጨነቅ ነበር […]

ሱዳን ከዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ጋር ለመተባበር መዘጋጀቷን ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሀማዶክ ተናገሩ::

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 9፣ 2013  ሱዳን ከዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ጋር ለመተባበር መዘጋጀቷን ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሀማዶክ ተናገሩ:: ሀምዶክ በሳምንቱ መጨረሻ የአይ.ሲ.ሲ ዋና አቃቤ ህግ የሆኑትን ፋቱ ቤንሱዳን ተቀብለው አነጋግረዋል ነው የተባለው፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ ሱዳንን የጎበኙት አቃቤ ህጓ በሀገሪቱ በካቢኔ ጉዳዮች እና በፍትህ ሚኒስቴሮች አስተባባሪነት የተዘጋጀውን ስብሰባ ከጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሀምዶክ ጋር አካሂደዋል፡፡ የቤንሱዳ […]