loading
ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ትምህርት ለማስጀመር መዘጋጀቱን ገለፀ::

አዲስ አበባ፣ መስከረም 26፣ 2013 ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ትምህርት ለማስጀመር መዘጋጀቱን ገለፀ:: ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል ታሳቢ ባደረግ መልኩ ትምህርት ለማስጀመር የሚያስችለውን ዝግጅት ማድረጉ ገልጿል። የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሉኡካን በዩኒቨርሲቲው የተማሪዎች ቅበላን በማስመልከት የመስክ ምልከታ አካሂዷል። በሚኒስቴሩ የከፍተኛ ትምህርት አካዳሚክ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጄኔራል ዶክተር ኤባ ሜጀና በወቅቱ እንደተናገሩት  ፤ዩኒቨርሲቲው ወረርሽኙን ለመከላከል ያከናወነው ተግባር የሚበረታታ ነው። […]

በሀገሪቱ የሳይበር ጥቃት ከተቃጣባቸው ተቋማት የሚዲያ ተቋማት በ2ኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኙ ተገለፀ፡፡

አዲስ አበባ፣ መስከረም 27፣ 2013 በሀገሪቱ የሳይበር ጥቃት ከተቃጣባቸው ተቋማት የሚዲያ ተቋማት በ2ኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኙ ተገለፀ፡፡የኢንፎርሜሽን መረብ ደሕንነት ኤጀንሲ እና የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን የመገናኛ ብዙሃን ተቋማትን ከማንኛውም የሳይበር ጥቃት ለመከላከል የሚስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡የኢንፎርሜሽን መረብ ደሕንነት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ሹመቴ ግዛው እና የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ጌታቸው ድንቁ ስምምነቱን ፈርመዋል። የመግባቢያ […]

የአልበሽር ጠበቆች ቅሬታ::

አዲስ አበባ፣ መስከረም 27፣ 2013 የአልበሽር ጠበቆች ቅሬታ::በአቃቤ ህግ ቅር የተሰኙ የአልበሽር ጠበቆች ችሎት ረግጠው ወጡ:: የቀድሞው የሱዳን ፕሬዚዳንት ኦማር ሀሰን አልበሽር ተከላካይ ጠበቆች አቃቤ ህግ አድሏዊ የሆነ ክርክር አቅርቦብናል ሲሉ ከሰዋል፡፡ በዚህም ምክንያት ከፕሬዚዳንቱ ጠበቆች መካከል የተወሰኑት የዕለቱን ክርክር በመተው ችሎቱን ረግጠው መውጣታቸው ተሰምቷል፡፡ አፍሪካ ኒውስ እንደዘገበው አልበሽር በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ሆነው ቢገኙ እስከሞት […]

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አመራሮች የምርጫ ቦርድን የምርጫ ዝግጅት ጎበኙ::

አዲስ አበባ፣ መስከረም 29፣ 2013 የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አመራሮች የምርጫ ቦርድን የምርጫ ዝግጅት ጎበኙ::የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎና የምክር ቤት አመራሮች የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የምርጫ ቅድመ ዝግጅትን እየጎበኙ ነው። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛው አገር አቀፍ ምርጫ የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ የመከላከያ መንገዶችን በመተግበር እንዲካሄድ ከጤና ሚኒስቴር የቀረበለትን ምክረ ሃሳብ በተጨባጭ በማጤን […]

ናይጄሪያዊቷ እንስት የዓለም የንግድ ድርጅትን ለመምራት ጫፍ ላይ ደርሰዋል::

አዲስ አበባ፣ መስከረም 29፣ 2013 ናይጄሪያዊቷ እንስት የዓለም የንግድ ድርጅትን ለመምራት ጫፍ ላይ ደርሰዋል:: የቀድሞዋ የናይጄሪያ የገንዘብ ሚንስትር ንጎዚ ኦኮንጆ ከደቡብ ኮሪያዋ ተፎካከሪያቸው ጋር የመጨረሻውን ዙር ውድድር ተቀላቅለዋል፡፡ የሃርቫርድ ዩንቨርሲቲ ምሩቅ የሆኑት ኦኮንጆ እና የመጨረሻው ዙር የደረሱት የኬንያ፣ የሳኡዲ አረቢያ እና የእንግሊዝ ተወዳዳሪዎችን በልጠው በመገኘታቸው ነው፡፡ ሀገራቸውን ደቡብ ኮሪያን በገንዘብ ሚኒስትርነት እያለገሉ የሚገኙት ዩ ሚዩንግ […]

ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከህመማቸው አገግመው በሳምንቱ መጨረሻ ወደ ስራ ይመለሳሉ ተባለ::

አዲስ አበባ፣ መስከረም 29፣ 2013 ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከህመማቸው አገግመው በሳምንቱ መጨረሻ ወደ ስራ ይመለሳሉ ተባለ:: በቤተ መንግስታቸው ተወሽበው የከረሙት ፕሬዚዳንት ትራምፕ ከኮሮናቫይረስ ማገገማቸውን ሀኪሞቻቸው ተናግረዋል፡፡ በመጀመሪያ በዋይት ሀውስ ቀጥሎም በወታደራዊ ሆስፒታል ህክምናቸውን የተከታተሉት ትራምፕ በለይቶ ማቆያ ውስጥ ጊዜየን ማጥፋት አልፈልግም የምጫ ክርክሬን በፊት ለፊት ማድረግ እፈልጋለሁ ብለዋል፡፡ የአሜሪካ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ […]

13ኛው ብሔራዊ የሰንደቅ አላማ ቀን ተከበረ::

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 2፣ 2013 13ኛው ብሔራዊ የሰንደቅ አላማ ቀን ተከበረ::13ኛው ብሔራዊ የሰንደቅ ዓላማ ቀን “ሰንደቅ ዓላማችን ለሰላማችን፣ ለአብሮነታችንና ለሃገራዊ ብልጽግናችን!” በሚል መሪ ቃል ተከብሯል፡፡የሰንደቅ ዓላማ ቀኑ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት የስራ ሃላፊዎችን ጨምሮ አርበኞች እና ሌሎች እንግዶች በተገኙበት ነው የተከበረዉ፡፡ ቀኑ በየዓመቱ የተለያየ መሪ ቃል እየተቀረፀለት በፌደራል፣ በክልልና በሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች በዋናነት ስለሰንደቅ […]

ጠ/ሚ ዐቢይ እና የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ በጅማ ዞን ጉብኝት አደረጉ፡፡

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 2፣ 2013 ጠ/ሚ ዐቢይ እና የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ በጅማ ዞን ጉብኝት አደረጉ፡፡ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ የጅማ ዩኒቨርሲቲ የስራ እንቅስቃሴን ጎበብኝተዋል መሪዎቹ ዩኒቨርሲቲው የሚያካሂዳቸውን የምርምርና የግንባታ እንቅስቃሴዎች መጎብኘታቸውን ኢቢሲ ዘግቧል።በተያያዘም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድና የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በጅማ ዞን ጎማ ወረዳ ቡናን ወደ ውጭ በመላክ ስኬታማ የሆነ […]

በኢትዮጵያ ከ100 ሺህ ሰዎች አምስት ሰዎች በወባ በሽታ ሕይወታቸው እያለፈ መሆኑን ተገለጸ::

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 2፣ 2013 በኢትዮጵያ ከ100 ሺህ ሰዎች አምስት ሰዎች በወባ በሽታ ሕይወታቸው እያለፈ መሆኑን ተገለጸ::የወባ በሽታ ስርጭት ተመልሶ ማንሰራራቱን የጤና ሚኒስቴር አስታዉቋል፡፡ባለፉት ሁለት ዓመታት የወባ በሽታ ስርጭት ተመልሶ እየተንሰራራ መምጣቱን የገለጸዉ ሚኒስቴሩ ፤በሽታውን ለመከላከል አመራሩ፣ ህብረተሰቡና የጤና ባለሙያው በትኩረት እንዲሰሩም ተጠቁሟል። የጤና ሚኒስትር ዴኤታው ዶክተር ደረጄ ድጉማ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን ቦሰት […]

በከተማ ልማት ዕቅድ ላይ የሚመክረው ጉባኤ ጥቅምት 5 ቀን 2013 ዓ.ም በአዳማ ከተማ ይጀምራል::

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 3፣ 2013 በከተማ ልማት ዕቅድ ላይ የሚመክረው ጉባኤ ጥቅምት 5 ቀን 2013 ዓ.ም በአዳማ ከተማ ይጀምራል::”የብልፅግና ማዕከላት ከተሞች እና ተወዳዳሪ የኮንስትራክሽን እንዱስትሪን ለመገንባት በጋራ እንሰራልን”!! በሚል መሪ ሀሳብ ከጥቅምት 05 -07 2013 ዓ.ም ድረስ በአዳማ ከተማ የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሴክተር የቀጣይ 10 ዓመታት መሪ ዕቅድ ትግበራ ማስጀመሪያ ጉባኤ እንደሚካሄድ ታውቋል፡፡ የጉባኤው ዋና […]